26/12/2025
ሰበር ዜና
እስሪኤል ለ ሱማሊላንድ የ አገርነት ዕውቅና ሰጠች
This page is the place wher you get timely and accurate information about Ethiopia
26/12/2025
ሰበር ዜና
እስሪኤል ለ ሱማሊላንድ የ አገርነት ዕውቅና ሰጠች
26/12/2025
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ለጂፒኤስ የቴሌቪዥን ጣቢያ ማስጠንቀቂያ ሰጠ
***************************
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ባወጣው መግለጫ ላይ እንደጠቀሰው በሀገራችን የሃይማኖት እና የእምነት ነጻነት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ-መንግስት መረጋገጡ ይታወቃል፡፡
በዚሁ መሰረት በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/13 መሰረት የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ምዕመኖቻቸው ባሉበት ሆነው በመገናኛ ብዙኃን አስተምህሮቶቻቸውን እንዲከታተሉ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ፈቃድ ወስደው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ብሏል፡፡
ባለስልጣኑ በአዋጁ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት መገናኛ ብዙኃን ተግባሮቻቸውን ህግና ሙያዊ ስነ-ምግባርን ባከበረ አግባብ ስለማከናወናቸው ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ክፍተቶች እንዲታረሙ ግብረ መልስ ይሰጣል፤ እንደ ጥፋቶች ዓይነትም ተገቢውን አስተዳደራዊ እርምጃ ይወስዳል ነው ያለው።
በመሆኑም የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለጂስስ ፕሮፌቲክ ስፕሪት ቸርች (ጂፒኤስ የቴሌቪዥን ጣቢያ) በቀን 13/4/2018 ዓ.ም በማህበራዊ ገጾቹ ላይ ያሰራጨውን ፕሮግራም ከመገናኛ ብዙኃን አዋጅ 1238/13 እና አግባብነት ካላቸው ሕጎች አንጻር የክትትል ሥራዎችን ማከናወኑን ጠቁሟል፡፡
በዚህም ፕሮግራሙ በሀገራችን የሰላሌ አካባቢን ተገቢ ባልሆነ መልኩ መገለጹን ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን፣ በዚህም መሰረት ለጂፒኤስ የቴሌቪዥን ጣቢያ በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ የተጠቀሱ የሕግ ድንጋጌዎችን በመጣሱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶታል፡፡
በቀጣይም ከላይ የተጠቀሱትን ህጎች ጥሰው የተገኙ የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ላይአስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ ሲሆን መገናኛ ብዙኃኑ ያሉባቸውን ሃላፊነቶች ተገንዝበው በጥንቃቄና በሃላፊነት መንፈስ እንዲሰሩ ያሳስባል ብሏል በመግለጫው፡፡
26/12/2025
ከህብረተሰቡ ባህል፣ ሞራልና እሴት ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ሲያሰራጭ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- በማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ መልዕክቶች ተደራሽነታቸው የበዛ በመሆኑ በትውልዱ ላይ የሚያሳድሩት አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው፤ ማህበራዊ ሚዲያን በአግባብና በኃላፊነት መንፈስ ከተጠቀሙበት ትውልድን በስነ ምግባር ለማነፅና ለማፅናት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚኖረው ነው፡፡ ነገር ግን ከዚህ በተፃራሪ የተሰለፉ አንዳንድ ግለሰቦች ለማየትና ለመስማት አጸያፊ የሆኑ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶችን ሲሰሩ ይታያል፡፡
ከህብረተሰቡ ባህል፣ ሞራልና እሴት ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ሲያሰራጭ ከነበሩ ግለሰቦች አንዱ የሆነውን ነዋሪነቱ በን/ስ/ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 6 የሚገኝ ናትናኤል ባደግ ገብሬ የተባለን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር የዋለው የማህበራዊ ሚዲያን (YouTube እና tiktok platform) ን በመጠቀም በንግግር ልቅ ፆታዊ ግንኙነትን የሚያበረታታና የሚያስፋፋ አፀያፊ መልዕክቶችን ሲያሰራጭ በመቆየቱ ነው።
ተጠርጣሪው በተለምዶአዊው ንግግር ሊገለፁ የማይችሉ አስፀያፊ ቃላትን በመጠቀም በትውልዱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሲያሳድር እንደነበር እና መሰል ይዘቶችን በተደጋጋሚ ጊዜ በመስራት በማህበራዊ ሚዲያ (YouTube እና tiktok platform) በመጠቀም ሲያሰራጭ እንደነበር ፖሊስ አብራርቷል፡፡
ፖሊስ በቁጥጥር ስር በዋለው ናትናኤል ባደግ ወይም "የማህበራዊ ሚዲያ አንቂ ወይም ይዘት ፈጣሪ ነኝ" በሚለው ግለሰብ ላይ ምርመራ ጀምሯል። በአንዳንድ ኃላፊነት በማይሰማቸው ግለሰቦች በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከህብረተሰቡ ሞራል ባህልና እሴት ባፈነገጠ ሁኔታ አሉታዊ መረጃዎች እየተሰራጩ መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ በማህበረሰቡ በተለይም ታዳጊ በሆኑ ህፃናት ሥነ-ልቦናና ሞራል ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ መሆኑን ገልፆ በቀጣይም ተመሳሳይ ድርጊት ውስጥ በሚገቡ ግለሰቦች ላይ ተገቢውን ህጋዊ ርምጃ እንደሚወስድም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ያሳስባል፡፡
*
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
“Protect with courage, Serve with Compassion!”
ይድረስ ለ ፌዴራል ፓሊስ ፥ለ አዲስ አበባ ፓሊስ፥ ለመረጃ እና ደህንነት አገልግሎት
መንግስት የመገናኛ ብዙሀን አጠቃቀም ለይ እያደረገ ስላለው ክትትል የሚያስመሰግን ነው በቀጣይ ሚዲያን በመጠቀም የውሸት አካውንት በመክፈት ጭምር በማናለብኝነት
የተቋማትን፥የባስልጣናትን፥የግለሰቦችን፥የሀይማኖት መሪዎችን ወ ዘ ተ በመስደብ ስም በማጠልሸት ለይ የተሰማሩ ግለሰብ እና ቡድኖች ለይ ክትትል እና እርምጃ ይወሰድ። share share share
25/12/2025
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለፈረንጆች የገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለፈረንጆች የገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፋት መልዕክት ፥ በመላው ዓለም የገናን በዓል ለሚያከብሩ የኢትዮጵያ ቤተሰቦች በሙሉ መልካም በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
ወቅቱ የሚያስታውሰን መልካምነት ድንበር ተሻጋሪ መሆኑን እና ተስፋን በጋራ መገንባት እንደምንችል ነው ሲሉም አውስተዋል።
14/09/2025
ግድባችን የመቻል ማሳያ ነው
12/09/2025
ሰባቱ የጉባ ብስራቶች 🔥
****************
በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት የሚተገበሩ ሰባቱ ግዙፍ ፕሮጀክቶች፤
✅የኒውክሌር ማበልጸጊያ
✅የጋዝ ፋብሪካ ማስመረቅ
✅የነዳጅ ማጣሪያ እውን ማድረግ
✅በአፍሪካ ግዙፉ አየር ማረፊያ
✅2ኛውን የጋዝ ፋብሪካ ግንባታ ማስጀመር
✅የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ማስጀመር
✅1.5 ሚሊዮን ቤቶች በመላው ሀገሪቱ ማስጀመር
እነዚህ ፕሮጀክቶች ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚፈልጉ ናቸው።
#ሜጋፕሮጀክቶች
12/09/2025
የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2 2018 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ በመስቀል አደባባይ የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሂዷል።
"በህብረት ችለናል " በሚል መርህ በተካሄደው መድረክ የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች እና ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የህብረት ተምሳሌት እና የጽናት ምልክት ነው ያሉት ተሳታፊዎቹ አንድነታችንን በማጠናከር በሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮችም በጋራ መቆም ይኖርብናል ብለዋል።
የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የላብ፣ የደም እና የእንባ ውጤት መሆኑን የገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር ዓባይ ናቸው።
ለድጋፍ ሰልፍ የወጡ የከተማዋ ነዋሪች የህብረት ስፖርት ሰርተዋል።
12/09/2025
ቡርኪና ፋሶ ለሁሉም የአፍሪካ ተጓዦች ከቪዛ ነፃ ጉዞን ፈቀደች
መስከረም 2/2018 ዓ.ም
ቡርኪና ፋሶ ለሁሉም የአፍሪካ ተጓዦች ከቪዛ ነፃ ወደ ሃገሪቷ መግባት የሚያስችል ፖሊሲን አስተዋውቃለች፡፡
ሰዎች እና ሸቀጦች ወደ ሀገሪቱ የሚገቡበትን ሁኔታ ይበልጥ ምቹ ለማድረግ እና ቃጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር በማለም የተወሰነው ይህ ውሳኔ፤ ተጓዦች ጉዟቸውን ለማፀደቅ በበይነ መረብ በማመልከት ያለ ምንም የቪዛ ክፍያ ወደ ሃገሪቱ ለመግባት የሚያስችላቸው ይሆናል፡፡
በዚህም ሃገሪቱ ለአፍሪካ ሃገራት የጉዞ መስፈርቶችን ካቀለሉ ከነ ጋና፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ጋር እንድትሰለፍ አስችሏታል፡፡
ውሳኔው ከፈረንጆቹ 2022 ጀምሮ ስልጣን ላይ ያሉትን የሃገሪቱ ወታደራዊ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬን የፓን አፍሪካኒዝም ሃሳብ የሚያንፀባርቅ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ይህ ውሳኔ የሃገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ለማሳደግ እና ባህሏንም በማስተዋወቅ ዓለም አቀፍ ትኩረትንም እንድትስብ ያደርጋል ተብሎ ታምኗል፡፡
ሆኖም የሃገሪቱ ውሳኔ ከጎረቤት ሃገሮቿ ጋር ያላትን ግንኙነት ስለማጠናከሩ እርግጠኛ መሆን እንደማይቻልም ዘገባው አመላክቷል፡፡
ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ሌላ ህብረት ለመፍጠር የምዕራብ አፍሪካ መንግስታት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ኢኮዋስ) ለቀው መውጣታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
12/09/2025
መልካም አዲስ ዓመት 2018 የሰላም የፍቅር የደስታ አመት ይሁንልን።
01/12/2021
አሜሪካ ቁማር ተበላች 😜
*********************
በኢትዮጵያ የተነሳው የ እንቅስቃሴ ተቀጣጥሎ እየሄደ ይገኛል ነገር ግን እነዲህ ባስ ብሎ ይመጣል ተብሎ አልተገመተም ፣ የ ኒጀር ,ማሊ ና ቡርኪናፋሶ ዜጎች 👇
"ለአፍሪካ ትክክለኛ ወዳጆች ራሺያ ና ቻይና ስለሆኑ ከምእራባውያን ጋር ያላቹን ነገር አቁሙ "
፡
ሲሉ መንግስቶቻቸው አስጠንቅቀዋል።
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹ኢትዮጵያን አትንኩ🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹