02/06/2026
Prosperity Party Yeka Woreda 02 Branch-ብልፅግና
ይሄ የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፌስቡክ ገፅ ነው!!
02/06/2026
02/06/2026
ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ መርጣለች ፤ የህዝብ ተሳትፎና የዲሞክራሲ ጉዞ
ምርጫ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታዋን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ታሪካዊ ፋይዳ አለው ።
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በሚሊዮን የሚቆጠሩ መራጮች ማልደው ተነስተው በየምርጫ ጣቢያዎቹ በመገኘት ቀጣይ እጣ ፈንታቸውን እና ሀገሪቱን ለሚቀጥሉት 5 ዓመታት የሚመራውን መንግስት ለመምረጥ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለመምረጥ ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ምዝገባ ማካሄዳቸው የሚታወስ ሲሆን የድምፅ መስጠት ሂደቱ ላይም ሕዝቡ ያሳየው ተሳትፎ እጅግ ከፍተኛ እና ታሪካዊ ነበር።
የዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሀገሪቱ የፖለቲካ እና የልማት ጉዞ ላይ ትልቅ ምዕራፍ የሚከፍት ሲሆን፥ ህዝቡ በነፃነትና በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ድርሻውን ተወጥቷል።
በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተስተዋለው የመራጮች ሰልፍ ህዝቡ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳየበት ሆኗል። በተለይም የሴቶች፣ የወጣቶች እና አካል ጉዳተኞች የመጀመሪያ ጊዜ መራጮች ተሳትፎ ከፍተኛ መሆኑ ተስተውሏል።
ይህ ምርጫ ከፖለቲካዊ ውሳኔነቱ ባሻገር በሀገሪቱ የኢኮኖሚ መረጋጋት፣ በማህበራዊ ልማትና በዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች ላይ ቀጣይነት ያለው እድገት ለማምጣት መሰረት የሚጥል ነው።
ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷ በራሷ፥ የዲሞክራሲ ጉዞዋ ወደ ኋላ የማይመለስ መሆኑንና በትክክለኛ መስመር ላይ እየተጓዘች ለመሆኗ ትልቅ ማረጋገጫ ነው።
02/06/2026
ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት፣ ዛሬ ጠዋት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ስራ አስጀምረናል።
ይህ ትልቅ ተነሳሽነት፤ የተራቆቱ አካባቢዎችን በዘመናዊ የአፈር ጥበቃ እና በወንዝ ማጣራት ወደ አረንጓዴ ስፍራዎች በመቀየር፣ የፍራፍሬ ፓርኮችን ከእግር ጉዞ እና ከብስክሌት መንገዶች ጋር በማቀናጀት መዲናችንን አድሷል።
በአጠቃላይ 22.25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት፤ የማይቆራረጥ የልማት ስራችን ህያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሃገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
01/06/2026
አዲስ አበባ እየመረጠች ነው!
ጨለማ ሳይበግረው የተሰለፈው የየካ ወረዳ 02 ሕዝብ የዴሞክራሲ ባለቤትነቱን በተግባር እያረጋገጠ ነው።
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው
#ምርጫ2018
#አዲስአበባ
#የካወረዳ02
01/06/2026
አዲስ አበባ እየመረጠች ነው !
የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጻቸውን ሰጥተዋል
01/06/2026
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Website
Address
Addis Ababa
