Sawla Town health office

Sawla Town health  office

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sawla Town health office, Government Organization, Gofa sawla, Addis Ababa.

01/01/2022

የደ/ብ/ብ/ሕ /ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ የሙያ ምዝገባና ስራ ፈቃድ መስጠት ጀምሯል።

26/12/2021

በሀዋሳ የአልትራሳውንድ ስልጠና
(Title-Basic Obstetrics ultrasound )
(ከታህሳስ 21-25/2014 ይሰጣል)
------------------------------------------------
To;- Medical Doctors,IESO,HO, Rad.Technologist ,
Midwifery
⏩Basic Obstetrics Ultrasound በሀዋሳ ከተማ ታህሳስ 21- 25/2014 አ.ም በስልጠና ማዕከላችን እና በተመረጡ ሆስፒታሎች የሚሰጥ ስለሆነ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
👉አሰልጣኞች:-ኤክስፐርት ሰፔሻሊስት ሀኪሞች።
#አዘጋጅ =Ethio-American Health Trainings & Consultancy Institution. + Stakeholders.
👉ምዝገባ - ለተከታታይ 5 ቀናት ብቻ::
🔑Certificate Will Be Awarded with 15 CEU. ለምዝገባ ይደዉሉ
📳 0941038774
0965412222
0462124400
👉የሀዋሳ አድራሻችን -ሀዋሳ አቶቴ ሰሊሆም ክሊኒክ በሚገኝበት ህንፃ ላይ -ሁለተኛ ፎቅ።

Photos from Sawla City Administration Gov't Communication Affairs Office's post 02/12/2021
Photos from SNNPR Health Bureau's post 26/11/2021
Photos from Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau's post 12/11/2021
03/11/2021

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የፖሊዮ ዘመቻ ክትባት አፈጻጸም እስከ ዛሬ (17/02/2014 ዓ.ም) ድረስ ያለው አፈጻጸም በወረዳ ደረጃ ስታይ

03/11/2021

የውሸት ሪፖርትን የሚልኩ ጤና ባለሙያዎችን በመደበኛ ፍርድ ቤት በወንጀል ህግ እንደሚጠይቁ አዲሱ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አስታወቁ
=============================
በቀን 23-2-2014 ዓ.ም ከአጠቃላይ ከመምሪያ ሠራተኞች ጋር ውይይት ያደረጉት የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ ታዬ በመምሪያው የረጅም ዓመት ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ያሉበት ተቋም መሆኑ እንደ መልካም አጋጣሚ ቢወስዱትም በሌላ በኩል ለጤና ስርዓቱ መሻሻል ስጋት ሊሆን እንደሚችል አስታውቀዋል።

የሠራተኞቹ የረጅም ዓመት በዘርፉ መቆየታቸው ባካበቱት ልምድ, ዕውቀት እና ክህሎት የጤና ስርዓቱን ለማቀላጠፍ ወሳኝ መሆኑን በውይይቱ አስታውሰው በተመሳሳይ ተቋሙን ከመልመድ የተነሳ መሠላቸቶች እንዳይኖሩ አሳስበዋል።

በመሪነት ቆይታቸው የመምሪያው ሠራተኞች ሠዓት አክባሪ; በሳምንታዊ ዕቅድ እና ሪፖርት የሚመሩ በተጨማራም በቡድን መንፈስ በጋራ ተቀናጅተው እንዲሠሩ በውይይት መድረኩ አደራ ብለዋል።

በንግግራቸው መሀል ሀገርን ለአደጋ ከሚዳርጉ ጉዳዮች መካከል አንዱ የውሸት ሪፖርት መሆኑን አንስተው። በጤናው ሴክተር የሚቀርቡ ሪፖርቶች እና መረጃዎች ቀጥታ ከሰው ሕይወት ጋር የተገናኙ ስለሆኑ የተሳሳተ ውሳኔ ላይ እንዳንደርስ የሪፖርቶች ሀቀኝነት ልዩ ትኩረት ሠጥተው እንደሚሠሩ አስታውቀዋል።

በንግግራቸው ከጤና ኬላ ጀምሮ የሚመጡ ሪፖርቶች ፍፁም እውነት መሆን እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
በውሸት ሪፖርት ጉዳይ በግልም ሆነ በጋራ የተሳተፉ ሁሉ በመንግስት ሠራተኞች ድስፕሊን መምሪያ ወይም በግምገማ እንዲጠየቁ ሳይሆን የሚደረገው በመደበኛ ፍርድ ቤት በወንጀል መሆኑን አበክረው ተናግረዋል።

በንግግራቸው መጨረሻም በዞኑ ያለ ማንኛውም የግልም ሆነ የመንግስት ጤና ባለሙያ ሠራተኛ ለስራ ስነምግባር ልዩ ትኩረት እንዲሠጡ አሳስበዋል።

ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ሁሉም ዳይሬክቶሬቶች የ90 ቀን ዕቅዳቸው ባቀረቡት መሠረት እንዲተገብሩ አስታውቀዋል።

Mobile uploads 03/09/2021
Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Website

Address

Gofa Sawla
Addis Ababa