Ethiopian Trading Businesses Corporation - ETBC

Ethiopian Trading Businesses Corporation - ETBC

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Trading Businesses Corporation - ETBC, Public & Government Service, Addis Ababa.

30/05/2026
30/05/2026

🫘 🌾 የሀገር ውስጥ ገበያን ከማረጋጋት እስከ ዓለማቀፋዊ አቅርቦት! 🫘 🌾

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በመሠረታዊ የእህል እንዲሁም የቡና ምርት ንግድ በሀገር ውስጥ አቅርቦት የህብረተሰቡን የምርት ፍላጎት ከማሟላትና ገበያን ከማረጋጋት ባሻገር የሀገራችንን የተፈጥሮ በረከቶች ለዓለም አቀፍ ገበያ የማቅረብ ድርብ ተልዕኮን በብቃት እየተወጣ የሚገኝ ልማታዊ የንግድ ተቋም ነው፡፡

🌾 በሀገር ውስጥ ገበያ
ለሀገር ውስጥ ገበያ የምናቀርባቸው ጥራታቸው የተጠበቀ ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ሽንብራ፣ባቄላ እና ሌሎች ሰብሎች የኢትዮጵያውያን የዕለት ተዕለት ገበታ ግብዓትና የምግብ ዋስትና መሠረት፤ ለአምራቹም የገቢ ምንጭ ናቸው፡፡ የኅብረተሰቡን የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ለማሻሻል በሀገር ደረጃ በተያዘው አቅጣጫ መሠረትም ጥራቱን የጠበቀና በንጥረ-ነገሮች የበለጸገ የስንዴ ዱቄት በማስመረት በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ የስነ-ምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ የበኩሉን አስተዋጽዖ እያደረገ ይገኛል፡፡

☕️ በዓለም ገበያ
ለዓለም ገበያ በከፍተኛ ጥራትና በተወዳዳሪ ዋጋ የምናቀርባቸው የላቀ ጥራት ያላቸውና ሀገራችን የምትታወቅባቸው ጥዑም የአረቢካ ቡናዎች፣ ለተለያዩ ዓለም አቀፋዊ የምግብ ማቀነባበሪያዎች ግብዓት የሚሆኑ የቅባት እህሎችና ጥራጥሬዎች የውጭ ምንዛሪ ምንጮች ናቸው፡፡

🔬 ዘመናዊ አውታሮች
የቡና ቅምሻ ላቦራቶሪን ጨምሮ ባሉን ዘመናዊ የምርት ማደራጃ አውታሮች በመታገዝ፣ አስተማማኝና ጥራቱን የጠበቀ ምርት እስከ መዳረሻው ድረስ እናቀርባለን፡፡

🤝 አብረውን በመሥራት ትርፋማነትዎን ያሳድጉ፤ የኅብረተሰብ አጋርነትዎንም ያረጋግጡ!

📞 ለተጨማሪ መረጃ፡ በስልክ ቁጥር +251939575757 ይደውሉ፡፡

29/05/2026

🛒 መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦችን በተመጣጣኝ ዋጋ!

ከሀገር ውስጥ እንዲሁም ከውጭ አምራቾች በጥንቃቄ ተመርጠው የገቡና በብዛትና በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረቡልዎትን የስንዴ ዱቄት፣ ማካሮኒና ፓስታ፣ ሩዝ፣ የምግብ ዘይት፣ የአትክልት ቅቤ፣ የወጥ ማጣፈጫዎች፣ ስኳርና ሌሎችንም የምግብ ሸቀጦች ከአለ በጅምላ መደብሮችና ከኮርፖሬሽኑ ሚኒ-ማርኬቶች ዛሬውኑ ይሸምቱ፤ ማዕድዎን ያድምቁ!

በደስታ ያብስሉ፣ በፍቅር ይመገቡ! ❤️

28/05/2026

✨ ንጹህ ቤትና አካባቢ የጤናማና ዘመናዊ ኅብረተሰብ መገለጫ ነው!

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአለ በጅምላ መደብሮቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ያቀረበልዎትን ጥራት ያላቸው የግልና የቤት ንፅህና መጠበቂያ ምርቶች በመጠቀም የራስዎንና የቤተሰብዎን ጤንነት ይጠብቁ፤ የመኖሪያና የሥራ አካባቢዎንም አንጸባራቂ ያድርጉ!

በመደብሮቻችን፡-
🧼 የገላ ሳሙናዎች እና ሻምፑዎች
🧺 የልብስ ሳሙናዎች እና ዲተርጀንቶች
🍽 የቤትና የወጥ ቤት ዕቃ ማጠቢያ ፈሳሽ ሳሙናዎች
🚽 የመጸዳጃ ቤት ፀረ-ጀርም ሳሙናዎችና ሌሎችንም የግልና የቤት ንጽህና መጠበቂያዎች ያገኛሉ፡፡

ከሀገር ውስጥ አምራቾች እና ከውጭ ሀገር በጥንቃቄ ተመርጠው የቀረቡ፣ ጥራታቸውን የጠበቁና ከበጀትዎ ጋር ፍጹም በሚስማማ ዋጋ የቀረቡ ምርቶቻችንን አሁኑኑ ይሸምቱ!

🌿 ንፁህ አካባቢ፣ ጤናማ ህይወት፣ የሀገር ኩራት!

ምርቶቹን በኮርፖሬሽኑ የአለ በጅምላ መደብሮችና ሚኒ-ማርኬቶች ያገኛሉ፡፡

26/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447 ኛው የኢድ አልአደሃ( አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

26/05/2026

በኢትዮጵያ የ118 ዓመታት የንግድ ሚኒስቴር ታሪክ የመጀመሪያው የንግድ ፖሊሲ

(አዲስ አበባ ፡ ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም) ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ወጥ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ በይፋ አፅድቃለች። ይህ የላቀ ስኬት ሀገሪቱ የንግድ ሚኒስቴር ከተቋቋመበት የ118 ዓመታት ረጅም ታሪኳ ውስጥ ራሱን የቻለና የነፃ ገበያ ሥርዓቱን የሚመራ ወጥ የፖሊሲ ሰነድ ያገኘችበት የመጀመሪያው ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።

ቀደም ሲል ወጥ የሆነ የንግድ ፖሊሲ አለመኖሩና የንግድ ሕጎች በተለያዩ አዋጆችና መመሪያዎች ውስጥ ተበታትነው መገኘታቸው በገቢና ወጪ ንግድ መካከል ቅንጅት እንዳይኖር ከማድረጉም በላይ፣ በንግድ ሥርዓቱ ላይ ፍትሃዊ ውድድር እንዲጠፋ፣ ሕገ-ወጥነት እንዲስፋፋና ሸማቾች ለከፍተኛ ምሬት እንዲዳረጉ በምክንያትነት ይጠቀሳል።

በአሁኑ ወቅት የጸደቀው ፖሊሲ እነዚህን መዋቅራዊ ክፍተቶች በመሙላት የሀገር ውስጥና የውጭ ንግድ አስተዳደርን በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት፣ የወጪ ንግድን በማዘመን ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ፣ የሀገር ውስጥ አምራቾችን በታሪፍና ማበረታቻዎች ለመደገፍ እንዲሁም የሸማቾችን መብትና ደህንነት ለመጠበቅ እጅግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

ይህ አዲስ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ በዋናነት በነፃ ገበያ ኢኮኖሚ፣ በትብብርና ቅንጅት፣ በግልፅነትና ተገማችነት እንዲሁም በፍትሃዊ ውድድር መርሆዎች ላይ የተገነባ ነው። የሰነዱ አጠቃላይ ይዘትም የሀገር ውስጥ የግብይት ሥርዓትን ማዘመን፣ የገቢና ወጪ ንግድ አስተዳደር ማዕቀፍን ማጠናከር፣ ፍትሃዊ ንግድን ማስፈንና የዲጂታል ንግድ (E-commerce) ሥርዓትን መገንባት ላይ ያተኩራል።

በአጠቃላይ ፖሊሲው በንግዱ ማኅበረሰብ ላይ ከፍተኛ መተማመንን በመፍጠር፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን በመሳብና የሀገሪቱን የንግድ ምህዳር ወደ አዲስ ምዕራፍ በማሸጋገር የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የተጣለ ትልቅ መሠረት ነው።

Photos from Ethiopian Trading Businesses Corporation - ETBC's post 25/05/2026

የኮርፖሬሽኑ ምርቶች በለሚ ሁለገብ ገበያ ማዕከል

በለሚ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ውስጥ ወደሚገኘው የኮርፖሬሽኑ የምርት መሸጫ መደብር ቁጥር 08 ጎራ ይበሉ፡፡ የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ይሸምታሉ፡፡

ለግብይት ምቹ የሆነ፤ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ ቦታ ያለው፡፡

ይምጡ! ይሸምቱ!

ሰሚት፣ ከሰሚት ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጠገብ፡፡

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 16:30
Tuesday 08:00 - 16:30
Wednesday 08:00 - 16:30
Thursday 08:00 - 16:30
Friday 08:00 - 16:30
Saturday 08:00 - 12:00