19/10/2025
በአባታችን ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት እጅግ አዝኛለዉ !!
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ እጅግ ትሁት ፣ የሀገር ወዳድ ምልክት ፣ በሁሉም ዘንድ የሚወደዱ ፣ የሚደመጡ እና የሚከበሩ አባታችን ነበሩ ።
ለቤተሰቦቻቸዉ ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸዉ ፣ እንዲሁም ለመላዉ የኢትዮዽያ ሕዝብ በከተማ አስተዳደራችን ስም ልባዊ መፅናናትን እመኛለዉ ።
ፈጣሪ አምላክ ነብሳቸዉን በአፀደ ገነት ያኑርልን ።
Lubbuun dabruu abbaa keenya dursaa M***ii Haaji Umar Idiriisitti baay'ee gaddineerra.
Dursaa M***i Haaji Umar Idiriis abbaa keenya baay'ee gara laafessa,mallattoo jaalala biyyaa,hunda biratti kan jaalataman,kan dhageettii qaban fi kan kabajaman turan.
Maatiisaaniif akkasumas uummata Itoophiyaa hundaaf maqaa bulchiinsa magaalaa keenyaatiin jajjabina hawwa.
Waaqni uumaa lubbuusaanii jaannata haa jiraachisu.
19/10/2025
#የተግባር ፣ የአመለካከት ጥራት በማስጠበቅ ፣ አመራሩ 7/24 እሳቤ ለውጤታማነት በመስራት ፣ እንደ አዲስ በማስፈንጠር ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በትጋት እንሰራለን!
በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ-03 አስተዳደር የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎችን የወረዳው አጠቃላይ አመራር በተገኙበት ግምገማ ተካሂዷል።
🖊የፓርቲ ተግባራትን
🖊 የስራ ዕድል
🖊የጤና መድህን
🖊የከተማ ግብርና ሌሎች ተግባራትን ጥቅል አፈፃፀም መገምገም ተችሏል::
18/10/2025
" ።"
==================================================
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የክ/ከተማ ለሱፐር ቪዥን የመጡ አካላት በቦሌ ወረዳ 03 አስተዳደር የሰንበት ገበያን በማየት ከምርት አቅርቦት ሁሉም አይነት ምርቶች መኖራቸውን ከወጋቸውም አኳያ ተመጣጣኝ መሆናቸውን በስታንዳርድ መሰረት ለህዝብ ተደራሽ እየሆነ እንዳለ አረጋግጠው ለወደፊ ደግሞ ከዚህ በበለጠ መሰራት እንዳለበት ለወረዳው የንግድ ፅ/ቤት እና በለድረሻ አካላት ምክረ ሀሳብን ሰጥተዋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 03 አስተዳደር የንግድ ፅ/ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተሰጠውን ግብረ መልስ በመቀበል የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋት በተመጣጣኝ ዋጋ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን የበለጠ ልንሰራ ይገባል ብለዋል ።
በወረዳው የሚገኙ የእሁድ ገበያዎች አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በአቅራቢያው በማገናኘት የዋጋ ንረትን ከማረጋጋት ባለፈ ሕገ-ወጥ ግብይትን ለመከላከል የንግድ አሻጥር በማስወገድ ሕጋዊ የግብይት ሥርዓትን በማስፈን እና ህብረተሰቡ ፍትሃዊ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ በቂ የሆነ የግብርና ምርትና የኢንደስትሪ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸጥ የንግድ ፅ/ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ።
#ጥቅምት 08/2018 ዓ.ም