01/06/2026
Prime Minister Abiy Ahmed (PhD) voted in Beshasha
----------------------------------------------------
Prime Minister Abiy Ahmed (PhD) cast his vote in the 7th general election in his birthplace, Beshasha.
30/05/2026
የቡና ጣዕምን በኤሌክትሪክ? የኦሪገን ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አዲስ ፈጠራ።
ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
የቡናን ጣዕም በትክክል ለመረዳትና ጥራቱን ለመለካት የነበረው ግምትና መወላወል ሊያበቃለት ነው ይሉናል የኦሪገን ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች። ለዚህ ደግሞ የቡናን የጣዕም ሚስጥር ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መለካት የሚያስችል አዲስ ስልት በማግኘታቸው እንደሆነ አስታውቀዋል።
ይህ ካፌዎችን፣ የቡና ቆዪዎችንና በቤታቸው ቡና የሚያፈሉ ሰዎችን ልማድ ሊቀይር የሚችል ግኝት በኬሚስትሪ ምሁሩ ክሪስቶፈር ሄንደን በሚመራ ቡድን ይፋ ሆኗል።
ተመራማሪዎቹ እንደገለጹት፤ በአንድ ስኒ ቡና ውስጥ የኤሌክትሪክ ፍሰት (Current) በማሳለፍ የቡናውን ጣዕም በሞለኪውል ደረጃ በከፍተኛ ጥንቃቄ መለካት ይቻላል።
ለዚህ ተግባር ተመራማሪዎቹ የተጠቀሙት "ፖቴንሺዮስታት" (Potentiostat) የተባለና አብዛኛውን ጊዜ ለባትሪና ለነዳጅ ሴል (Fuel cell) ምርመራ የሚያገለግል የላቦራቶሪ መሣሪያን ነው።
መሣሪያው የቡናውን ልዩ "የኬሚካል አሻራ" (Chemical fingerprint) መለየት የሚችል ሲሆን፤ ይህ አሻራ የቡናውን ጥንካሬና የቁሌቱን መጠን (Roastiness) በዝርዝር ያሳያል። እነዚህ ሁለት መለኪያዎች ደግሞ ማንኛውም ሰው ቡና ሲጠጣ የሚሰማውን እውነተኛ ጣዕም የሚወስኑ ቁልፍ ነገሮች ናቸው።
ለምን ይህ ዜና ትልቅ ትርጉም ኖረው?
ወጥነት ያለው ጣዕም፦ የቡና ቆዪዎችና ባሬስታዎች ሁልጊዜ አንድ ዓይነት ጥራት ያለው ቡና እንዲያቀርቡ ይረዳቸዋል።
ሳይንስና ጥበብ፦ የቡና አፈላልን ከባሕላዊ ልምድ ባለፈ ወደ ተረጋገጠ ሳይንሳዊ መረጃ ያሸጋግረዋል።
ቴክኖሎጂው፦ ቀደም ሲል ለኃይል ማመንጫ ምርምር ይውል የነበረ መሣሪያ አሁን ለጠዋት ቡናችን ጥራት መጠበቂያ መዋሉ አስገራሚ ነው።
አንድ ስኒ ቡና ውስጥ በመጨረሻ የምንጠብቃት ጣዕም በብዙ ሚስጥራዊና ረቂቅ ሁኔታዎች የተከበበች ናት፤ የውኃው ሙቀት፣ የዱቄቱ መድቀቅ እና መሸርከት፣ የቡናው ዝርያና የተገኘበት አካባቢ፣ የቁሌቱ ደረጃ እንዲሁም የማፍያ ሰዓቱ ጥቂቶቹ ናቸው። በእነዚህ ልኬቶች ላይ የሚደረግ ቅንጣት ታክል ለውጥ፣ ወደ ሲኒው የሚቀዳውን የቡና ጣዕም ሙሉ በሙሉ ሊቀይረው ይችላል። በመሆኑም ጥራት ላይ ትኩረት ለሚያደርጉ ካፌዎች እና ለተመረጡ ደንበኞቻቸው፣ የቡናን ወጥ ጣዕም ጠብቆ ማቆየት ሁልጊዜም በልምድና በትንንሽ ማስተካከያዎች የሚደረግ አድካሚ ትግል ነው።
በኦሪገን ዩኒቨርሲቲ የተገኘው ይህ የኤሌክትሮ-ኬሚካል ስልት ግን፣ ለዚህ ፈተና ጥልቅና የተራቀቀ መፍትሔ ይዟል። "ፖቴንሺዮስታት" መሣሪያው ቡናው ለተለካ የኤሌክትሪክ ቮልቴጅና ፍሰት የሚሰጠውን ምላሽ በመመርመር፣ ሊደረስባቸው የማይችሉ ረቂቅ የኬሚካል ልዩነቶችን በግልጽ ያሳያል።
ባጭሩ፦ ይህ ግኝት የቡናን ጥበብ በሳይንስ ሚዛን በመለካት፣ ግምትና ጥርጣሬ የሌለበትን ፍጹም ጣዕም ለማግኘት መንገድ ከፍቷል።
መረጃውን ያገኘሁት ከ Coffee Geography Magazine ሲሆን ፀሀፊው ደረጀ. ኤል. ገመዳ ናቸው።
በሳህለ ማርያም ገ/መ
29/05/2026
Spanish Cooperation Delegation Visits ECTA’s New Coffee interpretation center and Coffee Training Center, Highlighting Strides in Coffee History, Climate Resilience and Gender Equality
(May 29/2026: ECTA, ADDIS ABABA) — A high-level delegation from the Spanish Agency for International Development Cooperation (AECID) recently visited the Ethiopian Coffee and Tea Authority’s (ECTA) newly established Coffee interpretation center and Coffee Training Center (CTC). The visit marked a significant milestone in the ongoing partnership between Spain and Ethiopia, showcasing collaborative efforts to preserve Ethiopia's rich coffee heritage while modernizing the sector through sustainable development.
During the visit, Dr. Adugna Debela, Director General of ECTA, commended the Center as a premier model for exploring Ethiopia’s coffee history. He explained that the center meticulously archives the chronological journey of coffee from its historical origins to its global dissemination. Dr. Adugna emphasized that the facility serves as a vital hub for research and development—mapping the entire "seed to cup" value chain—while prominently highlighting the indispensable contributions of women to the sector. Looking ahead, he announced plans for the imminent expansion of the center and expressed sincere gratitude to the Spanish Cooperation and other international partners for their steadfast support.
Ato Shafi Omer, Deputy Director General of ECTA, echoed these sentiments, noting that the Center provides visitors with an accessible, comprehensive understanding of Ethiopia's diverse coffee varieties, distinct flavor profiles, and deep-rooted cultural traditions. He emphasized that before AECID’s vital assistance in constructing this showroom, the Authority lacked a dedicated space to display this heritage. Ato Shafi thanked the delegation for bringing this meaningful project to fruition and pledged ECTA's maximum effort toward implementing upcoming phases and continuously upgrading the Coffee interpretation center.
Providing technical context to the partnership, ECTA Project Coordinator and Executive Director of Women and Social Affairs, Ato Fitsum Mengesha, outlined the tangible impacts of Spain’s "Coffee Portfolio," which is deeply integrated into its Country Partnership Framework. A primary pillar is the flagship project, "Women’s Empowerment for Socio-Ecological Resilience of Coffee Value Chain against Climate Change in Ethiopia," co-funded by the European Union. Actively implemented around the Yayu Biosphere, this initiative safeguards smallholder farmers transitioning away from biodiversity-rich forest systems, while actively correcting gender disparities in a sector where women comprise 70% of the workforce but have historically been excluded from leadership and revenue.
Ato Fitsum also highlighted the successful implementation of the National Gender Equality Strategy, which serves as a guiding framework for empowering women and youth. Furthermore, he noted the establishment of a specialized call center designed to streamline information exchange from farms to export markets, backed by extensive regional and federal training capacity-building programs for female value-chain actors.
This comprehensive portfolio also features the initiative "Empowering Ethiopian Coffee: A South-South Approach to Climate Finance." This project future-proofs the sector by piloting innovative carbon-credit and agroforestry schemes for women producers in the Kaffa Zone and Oromia’s Yayu forest. Additionally, it leverages AECID’s extensive networks to facilitate vital knowledge transfers between Ethiopian institutions and coffee-producing countries. Through these combined efforts, the collaboration has successfully shifted the agricultural narrative from traditional aid to a sophisticated, sustainable model incorporating blockchain-level traceability, climate finance, and institutional gender mainstreaming.
Concluding the visit, the Spanish delegates expressed high praise for the center's development and its strategic focus on building climate resilience through women's empowerment. Reaffirming Spain's long-term commitment, the delegation encouraged ECTA to maintain its current momentum, promising continued, robust bilateral cooperation to drive prosperity across Ethiopia's coffee industry.
Reported by Tesfu Alemayehu.
28/05/2026
የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውን ችግኞች ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ ነው
ሚዛን አማን፤ ግንቦት 20/2018፦ የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል በምርምር ያወጣቸውን የቡና፣ የቅመማቅመም እና የፍራፍሬ ችግኞች ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑን ገለጸ።
ማዕከሉ በገበያ ተፈላጊ የሆኑ የካካዎ፣ የቫኔላና ሌሎች የቅመማቅመም ችግኞችን ለመጪው ክረምት ተከላ ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑን አስታውቋል።
የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ደረጀ ቱሉ (ደ/ር) እንዳሉት፣ ማዕከሉ የአርሶ አደሩን ምርታማነት የሚያሻሽሉና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ከ70ዐ ሺህ በላይ የቅመማቅመም ችግኞችን እያዘገጀ ይገኛል።
ችግኞቹ በመጪው ክረመት የሚተከሉ ሲሆን ለአካባቢ ሥነ ምህዳር ተስማሚና ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በክረምቱ የሚተከሉ ችግኞች ምርታማነታቸው ከፍ ያለ ከመሆኑ በላይ የአካባቢው ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ ተደማሪ አቅም እንደሚሆኑም አስረድተዋል።
የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አለምሰገድ ኃይለኢየሱስ በበኩላቸው ማዕከሉ ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ የቅመማቅመምና ሌሎች ችግኞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረቡን ተናግረዋል።
በዚህም የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ እንደቻለ አክለዋል።
ተግባሩን በማስቀጠልም ማዕከሉ በበጋ ወራት ያፈላቸውን ችግኞች ለክረምቱ ወቅት ተከላ ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ መሆኑንም ገልጸዋል።
በዞኑ የየኪ ወረዳ አርሶ አደር መሐመድ ታዬ እና አርሶ አደር አየለች አናሞ በበኩላቸው ከምርምር ማዕከሉ የሚቀርቡ ዝርያዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጡና ምርታማነታቸው ያደገ መሆኑን በተግባር ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።
ዘንድሮ በራሳቸው ያዘጋጁትንና በማዕከሉ የተዘጋጁ ችግኞችን በመትከል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ወደ ሥራ መግባታችውን አመልክተዋል።
ኢዜአ
28/05/2026
የብራዚል ሪል/Brazilian real መዳከም በቡና ዋጋ ላይ ጫና አሳደረ!!
ግንቦት 20/2018
በብራዚል የገንዘብ ምንዛሬ (ሪል) ላይ የታየው መዳከም፣ የዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ እንዲቀንስ ምክንያት ሆኗል። ረቡዕ ዕለት በዋለው የገበያ ግብይት፣ የሐምሌ ወር የአረቢካ ቡና ውል (KCN26) በ -4.15 (-1.51%) የቀነሰ ሲሆን፣ የሮቡስታ ቡና (RMN26) ደግሞ -47 (-1.34%) ዝቅ ብሎ ተዘግቷል።
የዋጋ መውረድ ምክንያቶች
• የምንዛሬ ተጽዕኖ፦ የብራዚል ሪል የመግዛት አቅም ባለፈው አንድ ሳምንት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ መዳከሙ፣ የብራዚል ቡና አምራቾች ምርታቸውን በስፋት ወደ ውጭ እንዲልኩ አበረታቷቸዋል። ይህ ከፍተኛ አቅርቦት ደግሞ በገበያው ላይ የዋጋ መውረድን አስከትሏል።
• የአቅርቦት ትንበያ፦ የተለያዩ ተቋማት (እንደ StoneX እና Marex ያሉ) የብራዚል የ2026/27 የቡና ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምርና ታሪካዊ ሪከርድ ሊሰብር እንደሚችል መተንበያቸው ለዋጋው መውረድ ሌላው ምክንያት ነው።
ዋጋውን የደገፉ ተቃራኒ ሁኔታዎች
ምንም እንኳን የሪል መዳከም ዋጋውን ቢያወርደውም፣ አንዳንድ ሁኔታዎች ደግሞ ዋጋው ከዚህም በታች ወርዶ እንዳይፈጠፈጥ ጥቂት የደገፉት ይመስላል፡፡
• የአየር ንብረት ስጋት፦ በቬትናም ያለው ደረቅ አየር በሮቡስታ ቡና ምርት ላይ ስጋት ፈጥሯል። በተጨማሪም የ"ኤል ኒኞ" (El Niño) የአየር ሁኔታ ክስተት በብራዚል የቡና ዛፎች አበባ በሚያወጡበት ወቅት ዝናብ ሊያዘገይ ይችላል የሚለው ስጋት ለዋጋው መረጋጋት ድጋፍ ሆኗል።
• የመጋዘን ክምችት መቀነስ፦ በአይሲኢ (ICE) መጋዘኖች ያለው የቡና ክምችት ላለፉት ሁለት ወራት እየቀነሰ መምጣቱ በገበያው ላይ ጥረት እንዳለ አመላካች ሆኗል።
• የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ መዘጋት፦ በዚህ መስመር ላይ ያለው የትራንስፖርት መስተጓጎል የመርከብ ዋጋን፣ የኢንሹራንስ እና የነዳጅ ወጪን በመጨመሩ፣ በተዘዋዋሪ የቡና ዋጋ ላይ የራሱ የሆነ ጫና ፈጥሯል።
የወደፊት እይታ
እንደ ዓለም አቀፉ የቡና ድርጅት (ICO) እና የዩኤስዲኤ (USDA) ዘገባዎች ከሆነ፣ የዓለም የቡና ምርት በ2025/26 የምርት ዘመን የ2 በመቶ ጭማሪ ሊያሳይ እንደሚችል ይጠበቃል። በተለይም የሮቡስታ ቡና ምርት የ10.9 በመቶ ከፍተኛ ጭማሪ ያሳያል ተብሎ ቢታሰብም፣ የአረቢካ ምርት ግን በ4.7 በመቶ ሊቀንስ እንደሚችል ተገምቷል።
ባጠቃላይ የቡና ገበያው በምንዛሬ መዋዠቅ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረቶች መካከል ሆኖ ከፍተኛ ትንቅንቅ እያስተናገደ ይገኛል።
ማጠቃለያ
ላለፉት ተከታታይ ወራት የሚታየው አለማቀፍ የቡና ገበያ ዋጋ እንደሚያመለክተው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀዛቀዘ እና ዋጋውም የመውረድ አዝማሚያን እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ምርትን በጊዜ ማውጣት እና ወደ ገበያ ማቅረብ ምትክ የማይገኝለት መፍትሄ ነው፡፡ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ግብይት ከአላስፈላጊ ኪሳራ ሊታደግ እንደሚችል ልብ ማለት ይገባል፡፡
ምንጭ አድርጌ የወሰድኩት https://www.barchart.com/ ነው፡፡
ሳህለማርያም ገ/መድህን
26/05/2026
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛ የኢድ አል-ዓደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ኢድ ሙባረክ!
አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር
26/05/2026
የተቀላቀሉ (Co-fermented) እና ጣዕም የተጨመረባቸው (Infused) ቡናዎች የደንበኞችን ፍላጎት እየቀየሩ ይሆን?
ከጥቂት ዓመታት በፊት እንደ ብርቱካን፣ እንጆሪ፣ ቸኮሌት፣ ቅመም ወይም የአበባ መዓዛ ያሉ የጣዕም መገለጫዎች (Tasting notes) አብዛኛውን የልዩ ቡና ተጠቃሚ ለማርካት በቂ ነበሩ። ዛሬስ?
ዛሬ ዛሬ ደግሞ ተጠቃሚዎች እንደ ዶናት፣ ከረሜላ፣ ትሮፒካል ፐንች፣ የእርጎ እና ፒች ሻይ የሚሉ ስያሜዎች የተለጠፉባቸውን ቡናዎች እየጠጡ ይገኛሉ። ብዙዎቹ ተጠቃሚዎችም እንደዚህ "ጠንከር ያሉ" እና ገንነው የሚወጡ የቡና ጣዕሞችን የመፈለግ አዝማሚያ ላይ እንዳሉ አንዳንድ በዘርፉ የተከተቡ ጽሁፎች ያመላክታሉ፡፡
ለዚህ ነው ጣዕም የተጨመረባቸው (Infused) እና ከሌሎች ፍራፍሬዎች ጋር አብረው እንዲብላሉ የተደረጉ (Co-fermented) ቡናዎች በአሁኑ ወቅት በልዩ ቡና ኢንዱስትሪ ውስጥ አወዛጋቢ አጀንዳዎች እየሆኑ የመጡት።
እነዚህ ቡናዎች ለምን በፍጥነት እየተስፋፉ መጡ?
ምክንያቱም እነዚህ ቡናዎች፦
• ለመረዳት ቀላል ናቸው
• ለገበያ ለማቅረብ ይመቻሉ
• በአእምሮ ውስጥ በቀላሉ ይታወሳሉ
ለአዳዲስ ተጠቃሚዎች፣ ንጹህና በባህላዊ መንገድ ታጥቦ የተዘጋጀ ቡና ጣዕሙ "ረቂቅ" ወይም ግራ የሚያጋባ ሊሆንባቸው ይችላል። ነገር ግን በአናይሮቢክ ዘዴ የፍራፍሬ ጣዕም ያለው ቡናስ? ይህንንም በተመለከተ የዘርፉ ሰዎች እንደሚሉት ተጽዕኖው ፈጣን ነው፣ ምላሹ ቅጽበታዊ ነው፣ የቀመሳ (Cupping) ልምድም አይጠይቅም፡፡ በመሆኑም ይህ ሁኔታ ደንበኞች "ጥሩ ቡና" የሚለውን ትርጉም የሚረዱበትን መንገድ እየቀየረው ነው።
ትልቁ ለውጥ፦
ዛሬ የቡናው ጣዕም ከቡናው መገኛ Origin/ "ይህ ቡና ከየትኛው አካባቢ የመጣ ነው?" ከሚለው የደንበኞች ፍላጎት ባሻገር "ጣዕሙ ምን ይመስላል?" የሚለው ጉዳይ መሰረታዊ ጥያቄ እየሆነ መጥቷል፡፡ ይህ ቀላል ሊመስል ይችላል፤ ነገር ግን የባለልዩ ጣዕሞች ቡና የንግድ ግንኙነት ወዴት ሊሄድ ይችል ይሆን የሚለውን ጉዳይ ከወዲሁ ለመገመት የሚያዳግት አይመስልም።
ይህ ማለት ግን ባህላዊ /Washed, unwashed ቡናዎች ችግር ይገጥማቸው ይሆናል ደግሞ ማለት አይደለም::
እንዲያውም ብዙ ልምድ ያላቸው የቡና ጠጪዎች ቀስ በቀስ ወደሚከተሉት እየተመለሱ ነው፦
• ወደ ንጹህ ጣዕም (Cleaner cups)
• ግልጽ ወደሆነ አዘገጃጀት (Transparent processing)
• የአካባቢን ለምነትና መዓዛ ወደሚያሳዩ ቡናዎች (Terroir-driven)
• ከከባድ ጣዕም ይልቅ ለጥራትና ለንጽህና ቅድሚያ መስጠት
እውነታው፦
ከፍራፍሬ ጋር አብረው የቦኩ (Co-fermented) ቡናዎች ልዩ ቡናን እየተኩት አይደለም፤ ይልቁንም የገበያውን አማራጭ እያሰፉት እንጂ።
የልዩ ቡና የወደፊት ዕጣ ፈንታ በባህላዊ መንገድ የታጠቡ ቡናዎች ወይም በጣም ኃይለኛ ጣዕም ያላቸው የተቀላቀሉ ቡናዎች መካከል ባለ የገበያ ጨዋታ ሜዳ መካከል ይመስላል፡፡ ይልቁንም የወደፊቱ ጊዜ የሚሆነው በሁለቱም መሃል ያለውን ሚዛን ለሚረዱ አምራቾችና ቆዪዎች ነው።
ለእርስዎ እንደ አንድ የዘርፉ ባለሙያ፤ እነዚህ Co-fermented እና ጣዕም የተጨመረባቸው (Infused) ቡናዎች የኢትዮጵያን ባለ ተፈጥሯዊ መዓዛ (Original Terroir) ሊፎካከሩ ይችላሉ ወይስ አዲስ የገበያ ዕድል ይፈጥራሉ?
ለእኔ ተፈጥሯዊ፣ ኦርጋኒክ፣ በርካታ ጣፋጭ፣ ውስብስብ እና ለዛ ያለውን የኢትዮጵያ ቡና ሊፎካከር አይደለም ጫፉ ሊደርስ አይችልም እላለሁ፡፡ ነገር ግን በጣም በጥራት እስከተዘጋጀ እና ባለልዩ ጣዕም የሚለውን መስፈርት እስካሟላ ድረስ፡፡
እናንተስ? እስኪ አስተያየት ስጡበት፡፡
በሳህለማርያም
24/05/2026
የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ ያለውን ተጽዕኖ ለማሳደግ.....
++++++++++++++
የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ ያለውን ተጽዕኖ ለማሳደግና የገበያ ተደራሽነቱን ለማስፋት የተለያዩ ስትራቴጂዎች ተነድፈው እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ በዘርፉ በዓለም ገበያ የኢትዮጵያን ድርሻ ይበልጥ ለማሳደግ በተለይ በምርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ትልቋ የቡና አምራችና ላኪ ሀገር ስትሆን፣ በአሁኑ ወቅት የቡና ምርት ጥራትና የገበያ ተጽዕኖዋ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ፣ አቅማቸውን መገንባትና የቡና ጥራትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው፡፡ በዓለም አቀፍና በአፍሪካ ደረጃ ያላትን የገበያ መዳረሻ ለማስፋፋት ስትራቴጅዎች ተነድፈው መተግበራቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ከፍተኛ መለኪያ የተቀመጠለት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በየካቲት ወር 2027 ዓ.ም 4ተኛውን የአፍሪካ የቡና ሳምንት በአዲስ አበባ የምታዘጋጅ ሲሆን፤ ይህም በቡና የሚኖረውን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው፡፣ በተለይም አነስተኛ አምራቾችን ለማበረታታት፣ የቡና ምርት ጥራትን ለመጠበቅና አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ሲሉም ገልጸዋል።
ጋዜጣፕላስ