Finote Tibeb ፍኖተ ጥበብ

Finote Tibeb ፍኖተ ጥበብ

Share

ሚሊዮን በለጠ አሰፋ

02/06/2026

https://vt.tiktok.com/ZSxTsujAY/
..
ይግባኝ ! ፪
ይግባኝ ለሥላሴ ፥ ለአጋእዝተ ዓለም ፤
ሰማየ ሰማያት ፥ ላለው በአርያም ፤
ምንም ሳላንዛዛ ፥ መግቢያና ሐተታ ፤
በአጭሩ አቀርባለሁ፥ ጥያቄ አቤቱታ ።
የምንሰማውና የምናየው ሁሉም ፤
ከአእምሮ በላይ ነው ፥
. . . ሕማም ማስከተሉም፤
በዚህ በእኛ ዘመን እየሆነ ያለው ፤
የአጼዎቹ ጊዜ አይወዳደረው ፤
ወያኔና ደርግም አይስተካከለው ፤
ከግራኝ በባሰ ፣ ከጣሊያን በከፋ ፣
ከዮዲት ጉዲትም ፥ከድርቡሽ በሰፋ ፤
ስንቱ ተቃጠለ ፥ ስንት ሰው ነደደ ፤
እልፍ ሰው ተገድሎ ፥ ቀሪው ተሰደደ ፤
የምድራዊው ችሎት፥ ፍርድ ተንጋደደ፤
አቤት የምንለው ፥ ስለሌለ ሰሚ ፤
ደረሰብን በደል ፥ ዘግናኝ አስቀያሚ ፤
መዶሻ ሚዛኑ ፥ የሹሙ መፈንጫ ፤
ሕጉ የላላ ነው ፥ ወንጀለኛ መቅጫ ።
የንብረቱ መውደም ፣ የቤቱም ፈረሳ ፤
የልባችን ቁስል ፥ መቼም ሳይረሳ ፤
ሀገር ሳትጠበን ፥ ሁሉም ተርፎ ሞልቶ ፤
ሀብትና ንብረቱ ፣ ጥሪቱ ፥
. . . ተነጥቆ ወይም ተቀምቶ ፤
የቀረ ሰው የለም ፥ ተገፍቶ ተገፍቶ ፤
እንጨቆረር ይሁን? ወይም ገጠር ገብቶ ።
ጌታ ሆይ! ፈጣሪ ፥ ልዑል እግዚአብሔር ፤
እንባችንን አብስ ፥ ሳይውል ወይ ሳያድር ።
ግልባጭ ለገልባጭ ፤ / ካለ
ይግባኝ ! ለአምላክ ፤
ብቻ በፈጠነ መፍትሔውን ላክ ::
መጨረሻ ላይም ፥ አለኝ መፈክር ፤
ቁመቱ ያጠረ ፥ ቅጥነቱ እንደ ክር ፤
የሀገር አፍራሹን ፥ አናቱን አፍርሳት !
አቃጥሎ ፈጀን ፥ የአመድ ልጅ እሳት ፤
አስከፍቶት ይሆን? ይግባኙ ለአራጄ ፤
ተናግሬስ ይሆን? በጣሙን ነድጄ!
ከሆነም አልፈራም ፥ ይኼውና እጄ ።

ሚሊዮን በለጠ አሰፋ፤ 18/9/2018
https://vt.tiktok.com/ZSxTxBsaF/

31/05/2026

Ingection exchange rate

07/05/2026

ይግባኝ! ለፈጣሪ፥ በላይ በሰማይ፤
ጊዜ ሳላጠፋ በጣም ባስቸኳይ ፤
አዝኖብን ለራቀን ለኃያሉ ጌታ ፤
መንበረ መንግሥቱ ፥ ከዙፋኑ ቦታ።
የፍታብሔሩ ፣ የሕግ ቍጥሩ ፥
. . . አያሻኝም ይቅሩ ፤
እንደሚከተለው ፥ ጉዳዬን ባጭሩ፦
በዚህ ብኩን ጊዜ በዚህ ከንቱ ዓለም፤
የሚነጥቀን እንጂ የሚሠጠን የለም።
ቀማኛዉም በዛ ፥ በሰበብ ባስባቡ ፤
ውሃና ኮረንቲ ፥ ይፋጃል ንባቡ ።
ቴሌም ብሶበታል ጭካኔውም በዛ ፤
ሙጭልፍ ያደርጋታል ካርድ ስንገዛ።
አድፍጦ ጠብቆ ፥ እንደ ሴቷ ነብር ፤
ደም መጣጭም አለ መዋጮና ግብር።
ነዳጅ ስለጠፋ ፥ ሰልፉም ስለ በዛ ፤
የታክሲ ወጪአችን እጅግ በጣም በዛ።
የቻርጅ መኪና፣ ሦስት እግር ኵርኵር ፤
ፋንዲያ የሚጥል ፥ ፈረስ ጋሪ ሳይቀር ፤
እያቆራረጡ ሲወርዱ ሲወጡ ከዚህና ከዛ፤
ሲያልቡን ይውላሉ ፥ በዋዛ ፈዛዛ ።
ግልባጭ ... ለገልባጭ /ካለ
ይግባኝ ለእግዚአብሔር ፤
ብቻ በፈጠነ መፍትሔ ወርውር ።

ሚሊዮን በለጠ አሰፋ ሚያዚያ 27 - 2018

28/04/2026
Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Website

Address

Addis Ababa