05/06/2026
Prospertiy Party Kolfe Keraniyo Sc Branch - ብልፅግና
Building a brighter future for Kolfe through economic growth, social equity, and community development
05/06/2026
በማያቋርጥ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ለሁሉም የምትሆን ዘመናዊና የበለፀገች ኢትዮጵያን መገንባታችንን እንቀጥላለን!
04/06/2026
በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት ባለ 7 ወለል ሕንጻ፦
04/06/2026
በሁሉም ፈጣሪ አምላክ ረድቶን 7ኛውን ዙር ምርጫ ባጠናቀቅንበት ማግስት ዛሬ 8ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ክፍት አድርገናል።
ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት ዛሬ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ ገንብተን በቴክኖሎጂ ተደራጅቶ 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግዱ መስኮቶች ያሉት፣ በ22 ተቋማትና በ114 አገልግሎቶች ስራ አስጀምረናል።
ማዕከሉ ከፍ ባለ ጥራት እጅግ ውብ፣ ፅዱ፣ አካታች የሆነ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ፣ የህፃናት ማቆያ ያለው፣ ለሰራተኞችም ለተገልጋዮችም ምቹ ሆኖ የተገነባ ነው።
በቀጣይም በርካታ አገልግሎቶችን ወደ መሶብ ማዕከል በማስገባት ነዋሪዎች ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኙ እናደርጋለን።
የከተማችን ነዋሪዋች መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አግልግሎት ለዘመናት አስልቺ ከነበረውና ውጣ ውረድ ከበዛበት እና በእጅ መንሻ ከተማረራችሁበት ቢሮክራሲ የሚያላቅቃችሁ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ! በማዕከላቱ በቦታ ሳትገደቡ በሚቀርባችሁ በየትኛውም ማዕከል በመገኘት ተገልገሉ።
ይህ ማዕከል ተጠናቆ ስራ እንዲጀምር ያስተባበራችሁትን በሙሉ ከልብ አመሰግናለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቧቿን ይባርክ!
04/06/2026
7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በታሪክ የሚዘከር ታሪካዊ አሻራ!
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ጉዞ ታሪክ ውስጥ የሚዘነጋ አይደለም። ይህ ምርጫ የፖለቲካ ተሳትፎ የጎለበተበት እና የሰላማዊ ውድድር ባህል የተጠናከረበት፣ የሕዝብ ድምፅ ክብር ያገኘበት ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ ይታወሳል።
የአንድ ሀገር ጥንካሬ በሕዝቦቿ ንቁ ተሳትፎ፣ በተቋማቷ ብስለት እና በሕግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ ነው። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫም ኢትዮጵያ እነዚህን እሴቶች እያጠናከረች ወደ ተሻለ የዴሞክራሲ ሥርዓት መጓዟን ያሳየ ወሳኝ አጋጣሚ ነው።
ምርጫው የተለያዩ ሀሳቦች በሰላማዊ መንገድ የተወዳደሩበት፣ ዜጎች የወደፊት ሀገራቸውን በድምፃቸው ለመቅረጽ የተሳተፉበት እና የዴሞክራሲ እሴቶች በተግባር የታዩበት ፍትሀዊ መድረክ ነው።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
04/06/2026
7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የተምሳሌት ጉዞ ማሳያ!
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ኢትዮጵያ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ታሪኳ ውስጥ አዲስና ብሩህ ምዕራፍ የከፈተችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። ይህ ምርጫ ተራ የድምፅ መስጠት ሂደት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ህዝብ በነፃነት፣ በሰላምና በብስለት የራሱን ዕድል በራሱ መወሰን እንደሚችል ለዓለም ያስመሰከረበት ታላቅ ሁነት ነው።
ምርጫው ኢትዮጵያ ማንኛውንም የውስጥ እና የውጭ ፈተናዎች እየተሻገረች ወደ ከፍታ የምታደርገው ግስጋሴ ለአፍታም እንደማይገታ ዳግም ያረጋገጠችበት ሲሆን፤ ለሀገራችን ሉዓላዊነት ተጠብቆ መዝለቅ የተጣሉ ፅኑ መሰረቶችን ጥንካሬም ማሳየት ችሏል፡፡
ይህ ታሪካዊ ምርጫ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድና በአጠቃላይ በአህጉሩ የእውነተኛ ዴሞክራሲ ተምሳሌት ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ በተግባር ያበሰረ ነው። የምርጫው ሂደት በሰላማዊ መንገድ መከናወኑ፣ የዜጎች በነፃነት የመሳተፍ መብት መረጋገጡ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች በሰለጠነ እና ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ሃሳባቸውን የሚያቀርቡበት አውድ መፈጠሩ የፖለቲካ ባህል ግንባታ ጉዞአችንን ከፍ አድርጎታል።
ኢትዮጵያውያን የሀሳብ ልዩነቶቻቸውን በግጭት እና በጦርነት ሳይሆን በንግግር፣ በውይይትና በህዝባዊ ውሳኔ መፍታት የሚችሉባቸው እሴቶች እንዳሏቸው ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማሳየት በኩልም 7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
03/06/2026
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ የተሰማውን ደስታ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ገልጿል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፀጥታ ኃይል አካላት እንዲሁም ሕዝቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ለተወጡት ሀገራዊ ኃላፊነት እና ላሳዩት ፅናትም ምክር ቤቱ ያለውን ምስጋና እና አድናቆት ገልጿል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው፣ “ልዩነቶቻችንን እና ችግሮቻችንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመፈታት በምርጫው የታየውን ሰላም በማስቀጠል የበኩላችንን ሚና እንወጣ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ እንቁም” ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Address
1000
