26/12/2024
በላቀ ዓቅም በወል እውነት ለሁለንተናዊ ልዕልና እየተጋን የተጀመረውን ብርሃናማ ጉዞ እናስቀጥላለን!!
ባሳለፍናቸው አምስት የለወጥ ዓመታት ዉስጥ እንደ ሀገር በገጠሙን ተግዳሮቶች ሳይንበረከክ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት የሚሆን ዘርፈ-ብዙ ስኬቶችን ማስመዝገብ ችለናል። ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ስድስት የለውጥ ዓመታት ያሳየው ዕምርታ በቀጣይ ኢትዮጵያ ለጀመረችው የከፍታ ጉዞ ስኬት አመላካችና ከብልፅግናችንን ማማ ላይ የሚያደረስ እውነተኛ ጉዞ ላይ መሆናችንን የሚያረጋግጥ ነው።
ብልፅግና እንደ ፓርቲ ከተመሰረተና የህዝብ ይሁንታን አግኝቶ የመንግስትነት መንበሩን ከተረከበ ጀምሮ ለህዝብ የገባውን ቃል በማክበር በርካታ ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ እምርታዎች ተመዝግበዋል። ባሳለፍነው የለውጥ ዓመታት የአፍሪካን ግዙፍ ኢኮኖሚ መገንባት የቻለው ፓርቲያችን ፈተናዎቻችን በድል በመሻገር ታላላቅ የዲፕሎማሲ ስኬቶችንም መቀናጀት ችሏል።
ብልፅግና ከመሰረቱ ሰው ተኮር በመሆኑ ቅድሚያ ለሰላም ትኩረት ይሰጣል። በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰላም ኖቤል ተሸላሚ በመሆን ዓለም አቀፋዊ ዕውቅናን የፓርቲያችን ፕሬዝዳንት ዶ/ር አብይ አህመድ አማካኝነት ማገኘት ተችሏል። ሰላም የብልፅግና ዕሴት በመሆኑ በመደመር ዕሳቤ በወንድማማችነትና እህትማማችነት የፀና ህብርብሔራዊ አንድነትን ለመገንባትና ሀገራዊ ሰላምን ለማረጋገጥ ተችሏል። በተለይም ''የአፍሪካን ችግር በአፍሪካዊ መፍትሄ'' በሚለው የፓርቲያችን አቋም ዓለም ዓቀፉዊ ዕውቅናን የተቸረ የእራስን ችግር በእራስ አቅም መፍታት የተቻለበት ዲፕሎማሳዊ ድል ተመዝግቧል።
በፓርቲያችን ሰውን ማዕከል ያደረገ የመደመር ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መርህ መሰረት በመዲናችን ብሎም በሀገር ደረጃ ያሉ የልማት ስራዎች የኢትዮጵያን መፃኢ የብልጽግና ጊዞ የሚያረጋግጡ ዓምዶች ናቸው። በተለይም በፓርቲያችን ፕረዚዳንት ዶ/ር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጭነትና ያላሰለሰ ድጋፍና ክትትል የተከናወኑ እንደ ኮይሻ፣ ሀላላኬላ፣ ጎርጎራን ጨምሮ የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ የበጋ ስንዴ ልማት፣ አረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋትና ዩ
የኮሪደር ልማት ስራዎች የብልጽግናችን መሰረት በማይናወጥ ዓለት ላይ መጣሉን የሚያረጋግጡ የትጋት ውጤቶች ናቸው።
በአጠቃላይ ብልፅግና የተናገረውን በተግባር የሚፈፅም ሰው ተኮር የሆነና ለሰላምና ልማት የሚተጋ ፓርቲ ነው። በመሆኑም የፓርቲያችን የለውጥ ትሩፋት የሆኑ በርካታ ሰው ተኮር ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ተግቶ ይሰራል፤ እየሰራም ይገኛል።
በብልጽግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት

26/12/2024