26/05/2023
የልደታ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ዋና የሥራ ሂደት
ላሎት አስተያየት Like በማድረግና ሐሳቦትን በመፃፍ ያካፍሉን
26/05/2023
26/05/2023
ማስታወቂያ ለንግድ ቤት ፈላጊዎች በሙሉ:-
5ኛው ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ የንግድ ሱቆች ጨረታ ሰነድ ከ19/09/15 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 28 የስራ ቀናት መሸጥ ይጀምራል
http://www.aahdab.gov.et
https://t.me/aahdabofficial
24/04/2023
የጋራ መኖሪያ ቤት ደርሷቸው እስካሁን ወደ ቤታችው ያልገቡ ነዋሪዎች እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ መግባት እንዳለባቸው ቢሮው እና ኮርፖሬሽኑ አሳሰቡ
የጋራ መኖሪያ ቤት ደርሷቸው እስካሁን ወደ ቤታችው ያልገቡ ነዋሪዎች እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ ወደ ቤታቸው መግባት እንዳለባቸው ያሳሰቡት በቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ በመግለጫቸው እንዳሉት ከፍሳሽ ፣ ከመንገድ፣ ከውሃና ከኤሌትሪክ እንዲሁም ከሳይት ወርክ አንፃር የተመረጡ ስራዎች ፣ ከሊፍት ገጠማና የውሃ ፓንፕና የሮቶ ተከላ ስራዎችን እየተፈተሸ የተጓደሉትን ለማስተካከል ቢሮው እና ኮርፖሬሽኑ ሌት ተቀን እየሰሩ ሲሆን ነዋሪዎችንም የአስተዳደሩ ፍላጎትን በመረዳት በራሳቸው አቅም መሰራት የሚችሉትን ስራዎች ወደየ ሳይቶቹ በመሔድ የማስተካከል ስራዎች መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል ፡፡
ነዋሪው ወደ የመኖሪያ ሳይቱ በጊዜ ባለመግባቱ ምክንያት እየደረሰ ያለውን ችግር በውል በመረዳት እያጋጠሙ ላሉ ችግሮችን ለመፍታት የመፍትሄ አካል በመሆንና መኖሪያ መንደራችውን በማልማት ለኑሮ ምቹና ጽዱ በማድረግ በከተማ ገፅታ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል ።
ቀበሌ ቤቶችን ጨምሮ ሌሎችንም የመንግስት ቤቶችን ይዘው የተቀመጡ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕድለኞች ቤቶቹን ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ማስተላለፍ እንዲቻል ከሰኔ ሰላሳ አስቀድመው መልቀቅ እንደሚጠበቅባቸው ያመላከቱት ዋና ዳይሬክቴሩ ዕድለኞቹ የአካባቢ ጽዳትና ውበት ስራን ጨምሮ የጸጥታ ስራዎችን በአካባቢው ከሚገኙ የጸጥታ ተቋማት ጋር መከወን እንዲቻል አስቀድመው መግባት ይጠበቅባቸዋልም ብለዋል ።
በቀጣይም ከተማ አስተዳደሩ በቅሩቡ ይፋ የተደረገውን የ70/30 የጋራ መኖሪያ ቤት አማራጭን ጨምሮ በከተማዋ የቤት ፍላጎትና አቅርቦትን ለማጣጣም ይሰራልም ብለዋል።
http://www.aahdab.gov.et
https://t.me/aahdabofficial
የ14ኛ ዙር የ20/80 እና የ3ኛው ዙር 40/60 የቤት ፕሮግራም የቤት ባለ ዕድለኞች ስም ዝርዝር መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።
http://www.aahdc.gov.et
09/09/2022
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የሴክተር መስሪያ ቤቶች የስራ እንቅስቃሴ በመገምገም የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል የምክክር መድረክ አደረገ።
አስተዳደሩ የተለያዩ ኮሚቴዎችን በማደራጀት ወደስራ እንዲገቡ በማድረግ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ገልጿል።
በምክክሩ ወቅት ንግግር ያደረጉት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሀይሉ ሉሌ እንደተናገሩት ከፊታችን በርካታ ሀገር አቀፍ በዓላት ከመምጣታቸው ጋር ተያይዞ ገበያው እንዳይረጋጋ የሚያደርጉ አካላት እንዳሉ በመገንዘብ ችግር ፈጣሪዎችን ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር ልንታገላቸው እንደሚገባ ገልጸው ከአምራቾች ጋር በመቀራረብ ምርቶችን ለህብረተሰቡ ማድረስ መቻል እንደሚገባ ገልጸዋል።
የአገልግሎት አሰጣጣችን በማሳደግ የህብረተሰቡን ፍላጎት ማሳደግ የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሀይሉ አገልግሎታችንን ከማሳደግ በተጨማሪ ለመከላከያ የሚደረጉ ድጋፎችን በማጠናከር የሀገር ህልውናን ማረጋገጥና ፍትሃዊ የሆነ መዘጋጃ ቤታዊ የስራ እንቅስቃሴን በመፍጠር ከህብረተሰቡ ጎን ልንሆን ይገባል ብለዋል።
የልደታ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉ እመቤት ታደሰ በበኩላቸው ሰላምን ከማረጋገጥ አንጻር ወጣቱና የተለያዩ አደረጃጀቶች ተሳታፊ በማድረግ ውጤትን ከማስገንዘብ አኳያ አበረታች መሆናቸውን ጠቁመው የምርት እጥረት ሳይፈጠር መጭዎችን በዓላት በሰላም ማክበር እንዲቻል ለማድረግ አመራሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የህብረተሰቡን ፍላጎት ያማከለ ስራ ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
ወ/ሮ ሙሉእመቤት አክለውም ለሀገር መከላከያ የሚደረጉ ድጋፎችን በማጠናከር ኃላፊነታችንን መወጣትና ከበዓል መምጣት ጋር ተያይዞ የተለያዩ የፍጆታ እቃዎችን አቅርቦትና ስርጭት በመቆጣጠር ህብረተሰቡን ልናገለግለው እንደሚገባ ተናግረዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት ሀገራችን የገጠማትን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ በሚደረገው ጥረት ከክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የአይነትና የገንዘብ ድጋፍ በመደረግ ላይ መሆኑን ጠቁመው ከድጋፎች ጎን ለጎን የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች የአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚታዩ ችግሮችን በማስተካከል ሁሉም መስሪያ ቤቶች ለህብረተሰቡ ፍላጎት መሳካት ኃላፊነታቸውን መወጣት ይገባናል ብለዋል።
09/08/2022
በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ዘመናዊ ቴክኖሎጅን በመጠቀም እየተገነቡ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶች በሚፈለገው ደረጃ በፍጥነትና በጥራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በከንቲባ አዳነች አቤቤ አስተባባሪነት እየተገነቡ ያሉ መኖሪያ 3ቱ ህንፃዎቹ እያንዳንዳቸው ባለ 11 ወለል ሲሆኑ በፍጥነት አጠናቆ ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ ያለምንም ፋታ 24 ስዓት እየተሰራ ይገኛል::
ግንባታው ሲጠናቀቅ 165 አባውራና እማውራዎችን ወይም 825 ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ያደርጋል ።
13/07/2022
ከ14ኛ ዙር የ20/80 እንዲሁም ከ40/60 3ኛ ዙር እጣ ማውጣት ጋር በተያያዘ ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮና የቤቶች ቢሮ የተለያየ እርምጃ የተወሰደባቸው አመራሮችና ባለሙያዎች ስም ዝርዝር
1ኛ. ዶ/ር ሙሉቀን ሃብቱ ቢሮ ሃላፊ ከሃላፊነቱ የተነሳ
በቁጥጥር ስር የዋሉ፡-
1ኛ. አብርሀም ሰርሞሎ የዘርፉ ምክትል ቢሮ ሃላፊ
2 ኛ . መብራቱ ወልደኪዳን :_ዳይሬክተር
3ኛ. ሀብታሙ ከበደ :_ሶፍትዌር ባለሙያ
4ኛ. ዬሴፍ ሙላት :_ሶፍትዌር ባለሙያ
5ኛ. ጌታቸው በሪሁን :_ሶፍትዌር ባለሙያ
6ኛ. ቃሲም ከድር :_ሶፍትዌር ባለሙያ
7ኛ. ስጦታው ግዛቸው :_ሶፍትዌሩን ያለማ
8.ኛ. ባየልኝ ረታ ፡_ሶፍትዌር ተቆጣጣሪ
9ኛ. ሚኪያስ ቶሌራ ፡_የቤቶች ኢንፎሜሽንና ቴክኖሎጂ ባለሙያ
10ኛ .ኩምሳ ቶላ ፡_ የቤቶች ኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ዳሬክተር
13/07/2022
የከተማ አስተዳደሩ የህዝብ ሃብት ለመጠበቅ ያደረገው ጥረት ሊመሰገን ይገባል፡፡
ፍትህን ያጓደለ ሲስተም ነው!!
ዶ/ር ሹመቴ ግዛው
በዛሬው እለት ሀምሌ 01/ 2014 የወጣውን የ 20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ የማጥራት ሂደቱን ሲያከናውን የነበረው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው እንደተናገሩት ከተማ አስተዳደሩን የህዝብን ሃብት ለመጠበቅ ያደረገውን እንደ ተቋምም እንደ ግለሰብም ላደረገው ጥረት ላመሰግን እፈልጋለሁ ብለዋል፡፡
ዶክተር ሹመቴ ግዛው ያነሷቸው ዋና ዋና ሃሳቦች
👉 ኢንሳ እንዲህ አይነት ስራዎችን እንዲመራ የህግ ሃላፊነትም ስላለበት ስራውን መርቶ እዚህ ደረጃ አድርሷል ብለዋል፡፡
👉 ሲስተሙ ከኑሮው ቀንሶ ተቸግሮ ሲቆጥብ የኖረውን ማህበረሰብ መብት እንዲያጣ የሚያደርግ በመሆኑ ሲስተሙ ተአማኒነት የሌለው ነው፡፡
👉 ሰው ነው ቴክኖሎጂን የሚገነባው ፤ ነገር ግን ፍትህን ያጓደለ ሲስተም ሆኖ ነው ያገኘነው፡፡
👉 ሲስተሙ የመልማት አለም አቀፍ ስታንዳርዱን ያልጠበቀና ሶስቱን አካላት ፤አልሚውን፤ ተጠቃሚውን እና አረጋጋጩን አካላት የቀላቀለ እንዲሁም ለምዝበራ ያጋለጠ ነው ብለዋል፡፡
👉 የዳታው አጠቃቀም ከእጅ ንክኪ ነፃ እንዲሆን የሚፈለግ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን እጅ በዝቶበት የነበረ መሆኑ ታይቷል፡፡
👉 ከዚህ የምንማረው ነገር ቢኖር በደረስንበት ደረጃ ተዓማኒ ያልሆኑ ነገር ሲገኝ አቁመን እንዲጣራና እርምጃ እንዲወሰድበት ማድረግ እንደሚገባና ሁልጊዜም ይህንን ማድረጋችንን መቀጠል እንዳለብን
👉 በተጨማሪም የአመራር ስነምግባርን ሟሟላት እንደሚያስፈልግ እንዲሁም ሰዎች የተሰጣቸውን የማገልገል እድል በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸውም ገልፀዋል፡፡
አቶ በሃይሉ አዱኛ ከኢንፎርሜሽንና ደህንነት ኤጀንሲ አጠቃላይ የአጣሪ ቡድኑን ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን
አጠቃላይ ሲስተሙ ፕሪፌሽናል በሆነ መንገድ የተሰራ አይደለም፡፡
👉 የሲተም አዘረጋግ አለም አቀፍ ስታንዳርዱን የጠበቀ አለመሆኑና የሚና ክፍፍል የሌለበት አሰራር መተግበሩ በማጥራቱ ታይቷል፡፡
👉 ሁሉም በአንድ ሰው የተሰራ ነበር፡፡ በአንድ ላፕቶፕ ከስራው ጀምሮ እስከ እጣ ማውጣቱ ድረስ ተከናውኖበታል፡፡
እጣው የወጣበት እለት ጭምር ኢንተርኔት አክሰስ ሲደረግ ነበር፡፡
የጥራት ፍተሻ እንዲደረግ የተጠየቀው አካል ራሱ ማንዴቱ የሌለው መሆኑም ታይቷል፡፡
የተተገበረው እጣ አወጣጥ ሶፍትዌር የተሻለ አማራጭ የነበሩትን ጭምር ያልተጠቀመና መረጣው መንገድ ችግር ያለበት ነው፡፡
የማበልጸግ ሂደቱ በሚከናወንበት ወቅት ከኢንተርኔት ጋር አክሰስ የተደረገ ሲሆን ይህም ፈፅሞ ተአማኒነቱን የሚያሳጣው መሆኑ
የተወዳዳሪዎች ዳታ እና ከባንክና ከቤቶች ተገኘው የአያያዝ ችግር ያለበትና ለቅየራ የተጋለጠ ነበር፡፡
የዳታ ዝርዝሩም ለ5 ቀናት በሰው እጅ ስር ነበር፡፡
ሲስተሙን ያለማው ሰው ለሌሎች የፈጠረው ዩዘር መጠቀሚያ በሚገባ ሲስተሙን እንዳያውቁ የሚከለክል ነበር፡፡
ይህ ግለሰብ በኮምፒውተሩ ስህተቱን ሪፖርት እንዳይደረግ ሚያደርግ ድብቅ ሶፍትዌር ጭኖ ነበር፡፡ በኋላ ግን አጥፍቶታል፡፡
የኮምፒውተሩ የድርጊት ሂደት ዝርዝር በሚታይበት ወቅት ያለፉት 8 ቀናት ኖርማል የነበረ ሲሆን በመጨረሻዎቹ ቀናት ግን ዳታ ማጥፋ የመጨመርና ማዛወር ስራ መሰራቱን ተረጋግጧል፡፡
ይህ ግለሰብ የኮምፒውተሩንም የሰዓት አቆጣጠር ሆነ ብሎ አንድ ቀን እንዲዘገይ በማድረግ ሁሉም ነገር ቀደም ብሎ እንደተፈፀመ እንዲደረግ በጥንቃቄ አከናውኗል፡፡
በአጠቃላይ ለውድድር ብቁ ናቸው ተብሎ የተገለፀው 79 ሺህ ያህል ሰዎች የነበሩ ሲሆን ሲስተሙ ግን በድብቅ ያጋጃቸው ሰዎች 172ሺህ ያህል ሰዎች ነበሩ፡፡
ከዚህ ውስጥ ደግሞ ገንዘብ ቀድመው አውጥተው የተዘጉ ፤የአመዘጋገብ ችግር ያባቸውና ብቁ ያልሆኑ ጭምር ተካተውበታል፡፡
ሲስተሙ የሚፈልገውን አካል እጣ እንዲያወጣ ተደርጎ የተሰራ ነው፡፡
ከባንክ የወጣው ዳታ ውስጥ የሌሉ አሸናፊዎች ተገኝተዋል፡፡
አጠቃላይ ሲስተሙ ከብልጸጋ እስከ ትግበራ ድረስ ሙሉ ለሙሉ ችግር ያለበት ስለሆነ በዚህ አይነት መንገድ የወጣ እጣ ኦፊሽያል አድርጎ መቀበል አዳጋች መሆኑን በምክረሃሳብ ደረጃ ቀርቧል!!
08/07/2022
ዛሬ የተላለፉ የጋራ መኖርያ ቤቶችን የተመለከቱ መረጃዎች፡-
👉 አሁናዊ የአንድ ካሬ የቤት ማስተላለፊያ ዋጋ
የሥራ አመራር ቦርዱ ታህሳስ 5 ቀን 2014 ዓ.ም በወሰነው መሠረት አሁን በሥራ ላይ ያለው አሁናዊ የአንድ ካሬ ማስተላለፊያ ዋጋ፡-
20/80 ቤት ልማት ፕሮግራም 7,997.17 ብር
40/60 ቤት ልማት ፕሮግራም 11,162.97 ብር ነው፡፡
👉 ለዕጣ የቀረቡ ቤቶች የሚገኙባቸው ሳይቶች፣ የቤት ዓይነትና ብዛት በተመለከተ
የ40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም
o አያት 2፤ ቦሌ በሻሌ፤ ቡልቡላ ሎት 2 ሲሆኑ
የ20/80 ቤት ልማት ፕሮግራም
o በረከት፤ቦሌ አራብሳ (ሳይት 3፤5፤6)፤ ወታደር፤የካ ጣፎ፤ ጀሞ ጋራ፤ ጎሮ ስላሴ፤ፉሪ ሃና እና ፋኑኤል
👉 በቤት ዓይነትና ብዛት ሲታይ
በ20/80 የቤቱ ብዛት ስቱዲዮ ፡-3318 ባለአንድ መኝታ ፡- 7171 ባለሁለት መኝታ፤- 8159 በድምሩ 18648 ናቸው፡፡
በ40/60 ባለአንድ መኝታ፤- 1870 ባለሁለት መኝታ 4220 እና ባለሶስት መኝታ 753 በአጠቃላይ በድምሩ 25491 ቤቶች ናቸው፡፡
👉 በዚህ ዙር ለዕጣ የቀረቡ ቤቶች የግንባታ አፈጻጸም ሁኔታ በጋራ መኖሪያና ንግድ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ በወጣ መመሪያ ቁጥር 3/2011 በሥራ አመራር ቦርድ በማስወሰን
የ20/80 ከ96% በላይ፣ በ40/60 ከ87% በላይ የግንባታ አፈጻጸም ያላቸው ቤቶች ለዕጣ ቀርበዋል፡፡
👉 የዚህ ዙር የዕጣ ተሳታፊዎች ሁኔታ (የቤት ፈላጊ ተመዝጋቢ ሁኔታ) የ20/80 ነባር ተመዝጋቢዎች (1997) በመመሪያው መሠረት ዝቅተኛውን የ60 ወራት ቁጠባ መጠን ያሟሉ ለእጣ ውድድር ብቁ የሆኑ እስከ የካቲት 21 2014 ዓ.ም ድረስ እና የ40/60 40% እና ከዚያ በላይ ቁጠባ ያላቸው እስከ የካቲት 21 2014 ዓ.ም የቆጠቡ ናቸው፡፡
👉 በእጣ ውስጥ የተካተቱት ተመዝጋቢዎችን በተመለከተ ከባንክ በተገኘው መረጃ መሠረት በ20/80 የቤት ልማት ፕሮግራም 27,195 እና 40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም 52,599 በአጠቃላይ 79,794 ተመዝጋቢዎች ለዕጣ ብቁ ሆነው በዚህ ዙር ዕጣ እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡ የዕጣ ተሳታፊዎች ሁኔታ ለዕጣ ከቀረቡ የቤት ዓይነቶች አኳያ በዝርዝር ሲታይ
👉 በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ የሚደረጉ ማህበረሰብ ክፍሎችን በተመለከተ በመመሪያ ቁጥር 3/2011 በተገለጸው መሠረት ከ20/80 ነባር ተመዝጋቢዎች (1997) እና 40/60 ተመዝጋቢዎች ውስጥ
የመንግስት ሠራተኞች 20 በመቶ፣
ሴቶች 30 በመቶ፣
አካል ጉዳተኞች 5 በመቶ እና አጠቃላይ ተመዝጋቢዎች 45 በመቶ በዕጣ የቤት ተጠቃሚዎች የሚለዩ ይሆናሉ።
👉 በከተማ አስተዳደሩ ፕሮጀክቱን ለመኖር ብቁ ለማድረግ ና ቤቶቹን ለማጠናቀቅ ከባንክ ቦንድ ብድር ብር 18.7 ቢሊዮን እና ለመሠረተ ልማት ግንባታ ከመደበኛ በጀት ብር 2.871 ቢሊዮን በድምሩ ብር 21.571 ቢሊዮን በሥራ ላይ ውሏል፡፡
👉 በ20/80 የቤት ልማት ፕሮግራም 27,195 እና 40/60 የቤት ልማት ፕሮግራም 52,599 በአጠቃላይ 79,794 ተመዝጋቢዎች ለዕጣ ብቁ ሆነው በዚህ ዙር ዕጣ እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡
👉 በዚህ ዙር ከተላለፉ ቤቶች ውስጥ ከዚህ በፊት በማጣራት ሂደት የተገኙ ቤቶች ለልማት ተነሺ ሲስተናገዱበት ቆይተው የቀሩት ተካተዋል፡፡
👉 የቤት ልማት ፕሮግራም ከጀመረበት አንስቶ በ17 ዓመታት ውስጥ ለህብረተሰቡ ማቅረብ የተቻለው 300 ሺህ ያህል ቤቶችን ብቻ ነው፡፡
👉 የቤት እጣ አወጣጡ እንደ ቅደም ተከተል ሲሆን በ20/80 ፕሮግራም የ97 ተመዝጋቢዎች ቅድሚያ አግኝተዋል፡፡
👉የባለ ሶስት መኝታ ቤት በተመለከተ ፕሮግራሙ ባለፈው ዙር በቦርድ ውሳኔ በመዘጋቱ በቀጣይ በልዩ ሁኔታ የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡
08/07/2022
ለረጅም ዓመታት በትዕግስት ገንዘባችሁን እየቆጠባችሁ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን በጉጉት የተጠባበቃችሁ የቤት ባለእድለኞች በሙሉ፤ እንኳን ደስ አላችሁ!!
የከተማ አስተዳደሩ የተረከበውን በርካታ ውስብስብ ችግሮች የነበሩባቸው ቤቶች እንዲሁም በተረከብነው ከ54 ቢሊዮን ብር በላይ የባንክ እዳ ተስፋ ባለመቁረጥ ይልቁንም በቁጭትና እልህ ሌት ተቀን በመረባረብ ከ21 ቢሊየን ብር በላይ በጀት በመጠቀም ለዛሬ ውጤት በመብቃታችን መላውን የከተማ አስተዳደራችን አመራሮችና ሰራተኞች በተለይም የቤቶች ልማትና የቤቶች ኮርፖሬሽን ሰራተኞችና አመራሮች ኮንትራክተሮች፤የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤እንዲሁም ሌሎች ለዚህ ስራ ስኬታማነት ሚናችሁን የተወጣችሁ በሙሉ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ!!
የከተማ አስተዳደራችን የከተማዋን የቤት ችግር ለመፍታት የተለያዩ የቤት ልማት አዳዲስ አማራጮችን በመዘርጋት የጀመረውን ርብርብ አጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን የከተማችን ነዋሪዎች እንደ ሁልጊውም ከጎናችን በመሆን የጀመርነውን ጉዞ ከጫፍ እንድናደርስ ጥሪዬን ማስተላለፍ እወዳለሁ !!
የሰሩ እጆችና ጉልበቶች ይባረኩ !!
Waggaa dheeraaf obsaan qarshii keessan qusachaa abbaa mana jireenyaa ta'uuf abdiin eeggachaa kan turtan abbootiin carraa manaa hundi baga gammaddan!!
Bulchiinsi magaalichaa manneen rakkoolee walxaxaa hedduu qaban fudhatee akkasumas gatii baankii biiliyoona 54 oliin abdii osoo hin kutatiin, caalatti ciminaa fi xiiqiin halkaniif guyyaa walta'insaan baajata qarshii biiliyoona 21 ol fayyadamuun bu'aa har'aarra ga'uun keenya bulchiinsa magaalattii hundaa fi hojjattoota keessattuu hojjattoota fi hooggantoota misooma manneenii fi korporeeshinii manneenii, kontiraaktaroota, Baankii Daldaala Itoophiyaa, akkasumas milkaa'ina hojii kanaaf shoora keessan kan bahattan hunda galata onnee koorraa madden isiniif dhiyeessa!!
Bulchiinsi magaalaa keenyaa rakkoo manaa magalattii furuuf haaromsa manneen garagaraatiif filannoowwan haaraa babal'isuun walta'insa eegale cimsee kan itti fufu yoo ta'u, jiraattonni magaalattii akkuma yeroo hundaa nu cinaa ta'uun adeemsa eegalle dhumarra akka geenyuuf waamicha koo dhiyessuun barbaada.
Harkii fi humnoonni hojjatan haa eebbifaman!!
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
20227/1000
