18/02/2026
ባለፉት አምስት አመታት ብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር ልማትን እንደ ዋና መርህ በመውሰድ ፖሊሲዎቹንና ፕሮግራሞቹን በዜጎች ሕይወት ላይ ቀጥተኛ እና ተግባራዊ ተፅዕኖ እንዲኖራቸው አቅጣጫ አስቀምጦ እየሰራ ይገኛል።
አቶ ሁሴን መሀመድ የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ዋና ስራ አስፈጻሚ
ፓርቲው ዓላማውን የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ማሻሻል፣ የስራእድል መፍጠር ማስፋፋት እና ማህበራዊ ፍትህ ማጠናከር ነው።
በወጣቶች ዘርፍ የሥራ እድል ፕሮግራሞች በተደራጀ መልኩ ተጠናክረዋል ቀጥለዋል ። አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመደገፍ፣ የሙያ ስልጠና በማቅረብ እና የፋይናንስ ድጋፍን በማስፋፋት ወጣቶች እራሳቸውን እንዲችሉ እና የሥራ አጥነትን እንዲቀንሱ አስተዋፅኦ አድርጓል።
በሴቶች አቅምን በማጎልበት የኢኮኖሚ ተሳትፎ በማሳደግ፣ የብድር እና የንግድ ድጋፍ በማቅረብ እንዲሁም በአስተዳደር እና በውሳኔ ሂደት ያላቸውን ተሳትፎ ማጠናከር ተፈጻሚ ሲያደርግ ቆይቷል ።
ይህ ሴቶች በማህበራዊና በኢኮኖሚ ዘርፍ እኩል ተሳታፊ እንዲሆኑ መሠረት ጥሏል። በማህበራዊ ዘርፍ ደግሞ አነስተኛ አቅም ላላቸው ዜጎች የተለያዩ የድጋፍ ፕሮግራሞች ተፈጻሚ አድርጓል። የጤናና የትምህርት አገልግሎቶች ማሻሻያ እና የችግር ጊዜ ድጋፍ በበለጠ አጠናክሯል። እነዚህ ሁሉ ልማት ቁጥር ብቻ ሳይሆኑ በሰው ሕይወት ላይ ታይቶ የሚሰማ ለውጥ እንዲያመጡ የተነደፉ እርምጃዎች መሆናቸውን ያሳያል።

18/02/2026
18/02/2026
18/02/2026
18/02/2026
17/02/2026