የልደታ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት

የልደታ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የልደታ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት, Government Organization, Addis Ababa.

24/07/2025

አስቸኳይ ማስታወቂያ

ኮሌጃችን ልዪ የክረምት ስልጠና የመጀመርያ ዙር ስልጠና ምዝገባ አጠናቀን ስልጠና በማሰልጠን ላይ መሆናችን ይታወቃል።

ስለዚህ ከዚህ በታች በተጠቀሱት የሙያ ዘርፍ ውስን ሰልጣኝ እሰከ ሀምሌ 21/11/2017 ዓ.ም በመምጣት እንድትመዘገቡ እናሳስባለን

1.Peachtree accounting =5 ሰልጣኝ
2.basic IFRS=5 ሰልጣኝ

Photos from የልደታ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት's post 24/07/2025

የስራ ስምሪትና ምግብ ዋስትና ዘርፍ የ2017 ዕቅድ አፈፃፀሙን በመገምገም የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ተወያየ።

በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ስምሪትና ምግብ ዋስና ዘርፍ የ2017 ዕቅድ አፈፃፀሙን በመገምገም የ2018 በጀት ዓመት ዕቅዱ ላይ ከዘርፉ የክፍለ ከተማ አመራርና ዳይሬክተሮች ጋር ተወያይቷል።

በውይይት መድረኩ በዘርፉ የሚገኙ የስራ ስምሪት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት፤የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት እንዲሁም የአንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።

በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት የስራ ዕድል ፈላጊ ዜጎችን በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት በመመዝገብ በስልጠና ውስጥ እንዲያልፉ በማድረግ በከተማዋ በሚገኙ የስራ ዕድል ፀጋዎች ለ366ሺ44 ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።

በከተማዋ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን በከተማ የልማታዊ ሴፍትኔት እንዲታቀፉ በማድረግ እና በተለያዩ የአካባበቢ ልማት ስራዎች ላይ በማሳተፍ 31ሺ2 ዜጎች ወደ ዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ መሸጋገራቸው ተገልጿል።

በተመሳሳይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎች እና በከተማዋ የሚገኙ ስደተኞችን ከሚደርስባቸው ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመታደግ በተሰራው ስራ አበረታች ለውጥ ማምጣት መቻሉ ተመላክቷል።

በበጀት ዓመቱ አንድ ማዕከላትን ሞዴል ፍረጃ በማጠናከር ሂደት አበረታች ውጤት ማምጣት መቻሉ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስታንዳርዱን የተመለከተ ጥናት ከማሰራት ባሻገር የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ከአንድ ዳሽ ቦርድ ጋር ማስተሳሰር መቻሉ ተነስቷል።

በሌላ በኩል በተያዘው የ2018 በጀት ዓመት ለ350ሺ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር 15ሺ ኢንተርፕራይዞችን በ105ሺ አንቀሳቃሾች ለማደራጀት ታቅዷል።

የውይይት መድረኩን የመሩት በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የስራ ስምሪትና ምግብ ዋስትና ዘርፍ ኃላፊ አቶ አስፋው ለገሰ በተጠናቀቀ የ2017 በጀት ዓመት የዜጎችን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንፃር አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን በመግለፅ በተያዘው የ2018 በጀት ዓመት ከተለመደው የአሰራር ዕይታ በተለየ መልኩ ዕቅዱን ከግብ ለማድረስ መትጋት ይገባል ብለዋል።

መረጃ የማጥራት ተግባሩን በማጠናከር በበጀት ዓመቱ ዜጎች በሚገባ ተጠቃሚ ስለመሆናቸው የማረጋገጥ ተግባር መከናወን እንደሚገባውም አቶ አስፋው አሳስበዋል።

Photos from የልደታ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት's post 24/07/2025

~ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ

የአምስት ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ኢንሼቲቭ አስተባባሪ አብይ ኮሚቴ የኢንሼቲቩን የአፈፃፀም ደረጃ በመገምገም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

በመድረኩ ኢንሼቲቩ ወደ ተግባር ከገባበት ጊዜ አንስቶ የተመዘገቡ ለውጦች እና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተካሂዶበታል።

በአዲስ አበባ ከተማ ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የኢትዮ ኮደርስ ኢንሼቲቩን ማሳካት እንደሚገባ የገለፁት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ አመራሩ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ተከታታይነት ያለው ግምገማ ማካሄድ ያስፈልጋል ብለዋል።

ኢንሼቲቩን ከክረምት የበጎ ፍቃድ መርሀ ግብር ጋር በማስተሳሰር እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሚገኙ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች በስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ መጭውን ዓለም አቀፍ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ ክህሎት ያለው ዜጋ ለመፍጠር እንደሚያስችልም ክቡር አቶ ጥራቱ ጨምረው ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አዋሌ መሐመድ በበኩላቸው ኢንሼቲቩ በሶፍትዌር ኢንዱስትሪው ያለውን የሰለጠነ የሰው ሀይል ፍላጎት በማሟላት ረገድ የራሱ የሆነ አውንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ አስተባባሪ አብይ ኮሚቴ አባል ተቋማት ኢንሼቲቩን ከግብ ለማድረስ በሚደረገው ጥረት የህብረተሰቡን ማህበራዊ አውድ በጠበቀ መልኩ በስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ ሂደት አስፈላጊውን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥሩ አረጋግጠዋል።

በቀጣይም የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባሩ ላይ በትኩረት በመስራት እና ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የሪፓርት ስርዓት በመዘርጋት ለዕቅዱ ስኬት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address

Addis Ababa