08/04/2026
በዛሬው እለት እሮብ የሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአካዳሚክ ኮሚሽን ስብሰባ አካሄደ። ኮሌጁ ተጠሪነቱ ለክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ እንደሆነ ይታወቃል እናም ለረጅም አመታት ተቋርጦ የነበረው የጤና ቢሮው በአካዳሚክ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ተሳትፎ ዛሬ በጤና ቢሮው ኃላፊ ክቡር ዶ/ር አብዲ አሚን ዳግም ነፍስ ዘርቶ ተመልሷል። ይህ ደግሞ ቢሮዉ ለኮሌጁ ምን ያክል ትኩረት እንደሰጠ ማሳያ ነው። በኮሌጁ ምቹ የስራ ከባቢን ለመፍጠርና ኮሌጁ የነበረውን ስመ ገናና ለመመለስ የታሰበና በቀጣይም የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ የታለመ ነው። ኮሌጁ ለ ዶ/ር አብዲ አሚንም ጊዜያቸውን አጣበዉ በመሃላችን በመገኘታቸውና ወደፊትም ከኮሌጁ ጎን እንደሚቆሙ ለሰጡን ቃል ያመሰግናል።
መጋቢት 29,2018 ዓ.ም
02/03/2026
The college would like to pass a warm wishing to our students who are going to take exit exam by tomorrow! Wish you all a good luck!
Kolleejin boru baratota isaatif exit exam warra fudhatanif carraa gaarii haawwaa!
ኮሌጁ ነገ የመዉጫ ፈተና ለሚፈተኑ ተማሪዎቹ በሙሉ መልካም እድልን ይመኛል።
01/03/2026
📘🎓The first batch of Harar Health Science College MSc students in Pediatrics and Child Health has successfully defended their thesis proposals.
The defenses were conducted in the presence of internal and external examiners, members of the College Academic Commission, and the wider college community.
This remarkable achievement marks a significant step forward in strengthening advanced pediatric and child health education and research. Congratulations to the students and appreciation to the academic staff for their guidance and commitment to excellence!
👏🎓 Well done and best wishes for the journey ahead!
ታሪካዊ የትምህርት ስኬት!
የሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሕፃናትና የሕፃናት ጤና (MSc in Pediatrics and Child Health) የመጀመሪያ ዙር ተማሪዎች የቴሲስ ፕሮፖዛላቸውን በስኬት ተከላክለዋል።
ይህ የቴሲስ መከላከል በውስጣዊና ውጭ ፈታኞች, በኮሌጁ የአካዳሚክ ኮሚሽን አባላት እና በሌሎች የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት ፊት ተካሂዷል።
ይህ ስኬት በሕፃናት ጤና ትምህርትና ምርምር ዘርፍ ከፍተኛ ዕድገትን የሚያመለክት ነው። ተማሪዎችን እንኳን ደስ አላችሁ፤ ለአስተማሪዎችም ለያዙት ትጋት እና ድጋፍ እናመሰግናለን።
👏🎓
📘🎓Barattoonni Marsaa jalqabaa MSc Pediyaatriksii fi Fayyaa Daa’immanii Kolleejjii Saayinsii Fayyaa Harar yaada qorannoo (thesis proposal) isaanii milkaa’inaan dhiheessaniiru.
Ittiisa qorannichaa kun qoratoota keessaa fi alaa, miseensota komishinii akkaadamikii kolleejjichaa, akkasumas hawaasa kolleejjii biroo duratti gaggeeffameera.
Milkaa’inni kun cimsina barnootaa fi qorannoo fayyaa daa’immanii sadarkaa olaanaa irratti tarkaanfii guddaa dha. Barattootaaf baga gammaddan; barsiisotaa fi hoggantootaafis galata guddaa dhiyeessina.👏🎓
17/02/2026
በዛሬው እለት ማክሰኞ የደም ልገሳ መርሐ ግብር በሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተከናውኗል።
Guyyaa har'a salaasa koolejji sayinsi fayyaa irratti dhiga arjomame jira!
ደም ዚኛ የቦርዲ መውለድቤ ደም የትኺሸዩዛል አያችሌ!
Dhigni kenya hadhoota dhalani dhiga barbaadanif haa ga'u!
ደማችን ይድረስ በወሊድ ደም ለሚያስፈልጋቸው እናቶች።
17/02/2026
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የረመዷን ፆም ወር በሰላም አደረሳችሁ!
ረመዷን ከሪም!!!
26/01/2026
የሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን የመጀመሪያ ሴምስቴር የእቅድ አፈፃፀም ግምገማን ማካሄድ ጀመረ።
ጥር 18፣ 2018 ዓ.ም.
የኮሌጁ አካዳሚክ ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሴምስቴር እቅድ አፈፃፀም ግምገማን ማካሄድ ጀምሯል። በበጀት አመቱ የኮሌጁ የአካዳሚክና የአስተዳደር የስራ ክፍሎች በአንድ-እቅድ-አንድ-ሪፖርት መርህ መሰረት ወጥነት ባለው መልኩ በርካታ ተቋማዊ ስራዎችን ሲፈፅሙ ቆይቷል።
የበጀት አመቱ እቅድ የኮሌጁ ተልዕኮን መሰረት በማድረግ የትምህርትና ስልጠና፣ ጥናትና ምርምር፣ እንዲሁም የማህበረሰባዊ አገልግሎት ተልዕኮዎችን በማካተት ዘርፈ ብዙ ተግባራት ሲከናወኑ ቆይቷል።
በተያዘው የግምገማ መርሃ ግብርም የሁሉም የስራ ክፍሎች አፈፃፀም አካላዊ ግምገማን በማድረግ በተጠናቀቀው ሴምስቴር የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል የነበሩ ክፍተቶች እና ደካማ ጎኖችን በመለየትና በማሻሻል በቀጣይ ሴምስቴር የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ አሁን የተጀመረው የአፈፃፀም ግምገማ ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
በግምገማውም ሁሉም የኮሌጁ ባለድርሻ አካላት እንደሚካተት ለማወቅ ተችሏል።
ግምገማው ከዛገሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።