20/04/2026
2 ቀናት ብቻ ቀሩት!
ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠው የምርጫ ካርድ መውሰጃ ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ዛሬውኑ የምርጫ ካርድዎን በመውሰድ መብትዎን ይጠቀሙ!
የሚመራዎን መንግስት በድምፅዎ መምረጥ ይችላሉ! የምርጫ ካርድ መያዝዎን ብቻ እርግጠኛ ይሁኑ!
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የሚከናወኑ ስራዎችን በዚህ የፌስቡክ ገፅ ይከታተሉ!!
20/04/2026
2 ቀናት ብቻ ቀሩት!
ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠው የምርጫ ካርድ መውሰጃ ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ዛሬውኑ የምርጫ ካርድዎን በመውሰድ መብትዎን ይጠቀሙ!
የሚመራዎን መንግስት በድምፅዎ መምረጥ ይችላሉ! የምርጫ ካርድ መያዝዎን ብቻ እርግጠኛ ይሁኑ!
08/04/2026
07/04/2026
ብልፅግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ሕልሞች እዉን ለማድረግ እየተጋ ይገኛል!
የኢትዮጵያ ሕልም ሦስት ትልሞችን እንደ ብሔራዊ ዓርማ አንግቧል። እነዚህም “ሰብአዊ ልዕልና” ፣ “ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት” እና “አፍሪካዊት ኃይል” ይሰኛሉ።
ሁሉም በጋራ ተስማምቶና ተግባብቶ የሚኖርበት፤ ነጻነት፣ እኩልነትና ፍትሕ የሰፈነበት ማኅበረሰብ ለመፍጠር የሚያስችል የፍትሕ ሥርዓትና አዎንታዊ ማኅበራዊ መስተጋብር ለመገንባት እናልማለን።
በዚህም የእያንዳንዱ ግለሰብና ቡድን መብቶቹ የወረቀት ጌጥ ሳይሆኑ በተጨባጭ የሚከበሩና የሚጠበቁ ይሆናሉ።
የፍትሕ ሥርዓታችን ሁሉንም ከአድሎ፣ ከጭቆና እና ከብዝበዛ የሚጠብቅ እንዲሆን እንሠራለን፡፡
#ምርጫ2018
06/04/2026
ብልፅግናን ይምረጡ፤ ምልክታችን የስንዴ ነዶ ነው!
በዛሬው እለት የብልፅግና ፓርቲ አመራሮቹ እና አባላቶቾ በተገኙበት ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማን በመወከል ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እና ለአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት የሚወዳደሩ እጩዎችን የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 በብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ተካሂዷል።
#ምርጫ2018
06/04/2026
በብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ወረዳ 07 ቅ/ጽ/ቤት "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር"!! በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት ዓመት የ3ተኛ ሩብ ዓመት የአባላት የማጠቃለያ ኮንፈረንስ በወረዳ ደረጃ ተካሂዷል።
የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ለማ ቱሉ
በኮንፈረንሱ ላይ ተገኝተው በመክፈቻ ንግግራቸው የፓርቲ ሥራዎች በአመርቂ ሁኔታ እንዲፈፀም በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና አባላት ርብርብ ትልቅ ድርሻ አላቸው በማለት ገልፀው በቀጣይም በጋራ እና በአንድነት የተጀማመሩ ሰፋ ስራዎች በጋራ በማጠናቀቅ የብልፅግናን ውጤታ ጉዞ እናስቀጥላለን ሲሉ ገልፀዋል።
የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ወንድሙ በበኩላቸው እንደ ከዚህ በፊት ሀላ አባላትን በማስተባበር መሰረታዊና ሰፋፊ ስራዎች በውጤት ተሰርተዋል የቀሪ ሶስት ወራት የፓርቲ ሥራዎች በተያዘላቸው ዕቅድ መሠረት እንዲከናወኑ እና በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ወቅትና ከምርጫ በኋላ እንደ አባል የሚጠበቅብንን ኃላፊነት በተገቢው በመወጣት ኢትዮጽያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ማሻገር ከሁሉም ብልፅግና አባል የሚጠበቅ ስራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በመጨረሻም በማጠቃለያ ኮንፍረንሱ መድረክ ላይ የ2018 በጀት ዓመት የሶስተኛ ሩብ አመት ሪፖርት አፈጻጸም ፣ የኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን ሪፖርት ላይ ውይይት በማድረግ የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል ብሎም የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ ማረም እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል ።
#ምርጫ2018
05/04/2026
05/04/2026
05/04/2026
በብልፅግና ፓርቲ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማን በመወከል ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎችን የማስተዋወቂያ ደማቅ መርሃግብር እያካሄደ ይገኛል!
#
#ምርጫ2018
04/04/2026
በቀጣይ አምስት ዓመታት፡- በሁሉም መስኮች ከተረጂነት በመዉጣት ኢኮኖሚያዊ ነጻነትን የተጎናጸፈች ኢትዮጵያን መገንባት!
ፓርቲያችን ብልፅግና በ7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በኢትዮጵያዊያን ይሁንታ መንግስት መመስረት የሚያስችል አብላጫ አባላጫ ድምጽ ማግኘት ከቻለ ሀገራችን የተሟላ ሉዓላዊነት እንድትጎናጸፍ የሚያስችላት የኢኮኖሚ ነጻነትን እንድታገኝ አበክሮ የሚሰራ ይሆናል።
ሀገራችን በሁሉም መስኮች ከተረጂነት ወጥታ፣ ያላትን ዕምቅ የልማት ዐቅም ወደ ምንዳነት ቀይራ፣ የአህጉራችንንም ሆነ የቀጣናችንን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ወደ ምትፈታበት ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ጠንካራ ሥራዎችን እንሠራለን።
ይህንን የነጻነት ጎዳና በምንጀምርበት ወቅት፣ በሌሎች ሀገራት የሚከሠቱ ችግሮች፣ የተሣሠሩ ተግዳሮቶችን እና ቀውሶችን በውስጣችን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ እንረዳለን፡ ነገር ግን ለእነዚህ ተግዳሮቶችና ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት የሚችል ዐቅም በመፍጠር፣ እየፈተኑን ያሉ ውጫዊ ተፅዕኖዎችን ለመቋቋም እንችላለን።
አብዛኞቹ የውስጥ ችግሮቻችን ከውጭ ጥገኝነት ጋር የተያያዙ ናቸው። ይህንን ውስብስብ ትሥሥር በመገንዘብ ዘላቂ መፍትሔዎችን እንቀርፃለን። በእርዳታ ላይ ያለንን ጥገኝነት እስከወዲያኛው እንዲያበቃ ለማድረግ እንሠራለን፡፡
04/04/2026
ብልፅግና ፓርቲ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤትና ለአዲስ አበባ ምክር ቤት የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ለሕዝብ አስተዋወቀ!!
02/04/2026
የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ዕለታዊ ኘሮግራሞች
ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሃገር!
02/04/2026
የለውጥ ጮራ ፈንጣቂ አንጸባራቂው ድል፤ መጋቢት 24 የብልጽግና አዋጅ፤ የነገዋ የኢትዮጵያ ብሩህ ደጅ!
መጋቢት 24 ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት አስመልክቶ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
#አዲስአበባ
#የለውጥጉዞ
#መጋቢት24