05/12/2025
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት-Ethiopian Political Parties Joint Council
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት-Ethiopian Political Parties Joint Council, Political organisation, Yeshi Building 7th floor, Addis Ababa.
05/12/2025
29/11/2025
የኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከ KrF ኖርዌይ ጋር በመተባበር የወጣቶች የፖለቲካ ተሳትፎን አስመልክቶ የተካሄደውን ውይይት በሚከተለው ማስፈንጠሪያ ገብተው ይከታተሉ ።
የኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከ KrF ኖርዌይ ጋር በመተባበር የወጣቶች የፖለቲካ ተሳትፎን አስመልክቶ የተካሄደ ውይይት#Youth participation
29/11/2025
የኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከ KrF ኖርዌይ ጋር በመተባበር የአካል ጉዳተኞች የፖለቲካ ተሳትፎን አስመልክቶ የተካሄደውን ውይይት በሚከለተው ማስፈንጠሪያ ገብተው ይከታተሉ ።
የኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከ KrF ኖርዌይ ጋር በመተባበር የአካል ጉዳተኞች የፖለቲካ ተሳትፎን አስመልክቶ የተካሄደ ውይይት with disabilities participation
29/11/2025
https://youtu.be/2945xwNYOlc?si=rHKNQhEUESvhySz5
የኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከ KrF ኖርዌይ ጋር በመተባበር የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎን አስመልክቶ የተካሄደ ውይይት#women participation
23/07/2025
ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመትከልና ሰላምን ለማፅናት ሚናችንን እናጠናክራለን -የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመትከልና ሰላምን ለማፅናት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ ገለጹ።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና ሰላም ሚኒስቴር በጋራ "ሰላምን በማጽናት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጁት ሀገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ መካሄድ ጀምሯል።
በመድረኩ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ታድመዋል።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ፥ ሰላም ለግለሰብ፣ ለማህበረሰብና ለሀገር ደህንነት መጠበቅ መሰረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።
ሀገር የምትጸናው በሰላም ነው ያሉት ሰብሳቢው፥ የዳበረ ዴሞክራሲያዊ ባህል፣ በዜጎች ቅቡልነት ላይ የተመሰረተ ሀገረ መንግስት ለመገንባትም ሆነ ለፖለቲካዊ መረጋጋት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
ነጻ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት እና ስልጡን የፖለቲካ ምህዳር ለሀገር ልማት ቀጣይነትና ዘላቂ ሰላም ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሀገሪቱ በሁሉም መስክ ወደ እድገት ጎዳና የምታደርገውን ጉዞ ለማሳካት አስተማማኝ ሰላም በመገንባት ሂደት የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
ግጭትን በዘላቂነት ለማስቀረት የፖለቲካ ፓርታዎች ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በማስረዳት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጠንካራ ዴሞክራሲ መሰረት ናቸው ሲሉም ተናግረዋል።
ሀገራዊ የፖለቲካ ሪፎርሙን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በፓርቲዎች መካከል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ የመሥራት ባህል መጎልበቱንም ገልጸዋል።
የጋራ ምክር ቤቱም የሀገርን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለማዳበር የላቀ ሚና እየተወጣ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
#ኢዜአ
20/07/2025
በኢትዮጵያ የዳበረ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን አቅም ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣የአፍሪካ አመራር ልዕቀት አካዳሚና የኔዘርላንድስ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የሦስትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በመግባቢያ ስምምነቱ ሥነ-ሥርዓት ወቅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓትን ለማዳበር በዕውቀት ላይ የተመሰረተ አመራርና አባላት አቅም መገንባት ያስፈልጋል።
ለዚህ ደግሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራር አባላትን አቅም ማጎልበት የሚያስችሉ ሥልጠናዎች ማዘጋጀት ወሳኝ ነው ብለዋል።
ምክር ቤቱ ከዚህ አኳያ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋርም መስራቱ በዕውቀት የሚመራ አመራር ለመገንባት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዳበረ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ አመራር አባላትን አቅም ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ የልህቀት አካዳሚው ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል።
ለዚህ ደግሞ አካዳሚው በአገር በቀል ዕውቀት የታገዘ የፖለቲካ ፓርቲዎች የስልጠና መመሪያና የአመራር ልማት ግንባታ እቅድና ስትራቴጂ ማዘጋጀቱንም ገልጸዋል።
የኔዘርላንድ መልቲ ፓርቲ ዴሞክራሲ ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ ተወካይ ይነበብ ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድብለ-ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በመድብለ ፓርቲ ስርዓት ውስጥ እየተገነባ ላለው ዴሞክራሲ ስርዓት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፥ከልህቀት አካዳሚው ጋርም በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በዛሬው ዕለት መፈራረማቸውን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ጠንካራ የመድበለ-ፓርቲ ሥርዓት በመገንባት ሂደት በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብረሃ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ በዚህ ረገድ ተቋማቱ በኢትዮጵያ የዳበረና የተረጋጋ የመድብለ-ፓርቲ ሥርዓት ለመገንባት የተፈራረሙትን ስምምነት ውጤታማ ለማድረግ አቅማቸውን አሟጠው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
#ኢዜአ
#ኢትዮጵያ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the business
Website
Address
Yeshi Building 7th Floor
Addis Ababa
