15/12/2022
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ነዋሪዎች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።
በመማር ማስተማሩ ዙሪያ ትኩረት ያደረገው ውይይቱ በደመቀ መልኩ ተጀምሯል።
06/4/2015
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት
Kutaa Bulchiinsa magaala lammii kuraa aanaa 10 bulchaa aanaa fi humna nama magaala Finfinnee waliin haala manneen barnootaa irratti jiraattoota maarisiseera jiraattonnis haala jiru irratti qophii tahu isaanii ibsaniiru
Guyyaa 06/04/2015/A.L.I
Waajjira Bulchiinsa fi Nageenya aanaa 10n
09/12/2022
ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከሰሚት ፖሊሰ ኮሚዩኒቲ ጋራ በመሆን በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ዉይይት አካሄዱ።
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከሰሚት ፖሊሰ ኮሚዩኒቲ ጋራ በመሆን በሶስቱ ቀጠናዎች ማለትም መሪ ለ፣የተባበሩት እና 72 ቀጠና ላይ ከሚገኙት ሊስተሮ፣ ፓርኪንግ እና መኪና እጥበት ላይ ከተሰማሩ አካላት ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ዉይይት አካሄዱ።
በዉይይቱ ላይ የተገኙት የወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቀነኒ ዋቅሹማ እንደገለጹት ወንጀልን ለመከላከል የሁሉም ህብረተሰብ ግዴታ እንደሆነና የአካባቢን ብሎም የሃገርን ሰላም ለማስጠበቅ ሁላችንም ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን መስራት ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም አንድ ወንጀል ተፈጸመ ማለት የእኛ እህቶችና ወንድሞች ተጎጂ እንደሚሆኑ ገልጸዉ ይህ ከመሆኑ በፊት በየአካባቢዉ የሚፈጸሙ ማንኛዉንም ወንጀል በጋራ ልንከላከል ይገባል ብለዋል። በምንሰራበት ቦታም ሆነ በምንቀሳቀስበት አካባቢ ወንጀል ሲፈጸም ካየን ወዲያዉኒ ለሚመለከተዉ አካል ማሳወቅ እንደሚገባም አክለዉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም የሰሚት ፖሊስ ኮሚዩኒቲ ምክትል ኢንስፔክተር አጥቃቸዉ ዘለቀ በበኩላቸዉ ወንጀለኛን ከአካባቢዉ ለማጥፋት ሁላችንም የበኩላችንን ማድረግ አለብን በማለት ገልጸዉ ወንጀል በአንድ ሰዉ ወይም ተቋም ብቻዉን መከላከል የሚችል አይደለም። ስለዚህ ሁላችንም እጅና ጓንት ሆነን ይህንን ድርጊት መከላከል አለብን ብለዋል።
ቀን 30/3/2015
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት
Kutaa Bulchinsaa magaala Lammii kuraa waajjirri bulchiinsa fi nageenya aanaa10 fi buufatni poolisii naannoo meetira 30 ,kutaa hawaasaa kan akka paarkingii,leestiroo,warra konkolaataa miiccan kanneen qaxanaa marii la,72 fi yetabaabaruut irraa dhufan waliin haala nageenya yeroo irratti waliin hojjechuudhaaf ega mari'ataniin booda uffata balaqqessituu fudhachuudhaan gara hojiitti seenaniruu.
Guyyaa 30/03/2015/A.L.I
Waajjira bulchiinsaa fi nageenya aanaa 10
29/11/2022
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በማሳጅ ቤቶች አገልግሎት የሚሰጡ አካላት ከነወሪዋች መካከል ተፈጠረው የነበረዉ አለመግባባት ላይ የወረዳው ሰላምና ጸጥታ አስተዳዳር ጽ/ቤት እና የ30 ሜትር ፖሊስ ኮምኒቲ ጋር ዉይይት አድገዋል።
ዉይይቱ ላይ የተሳታፉ አንድ አንድ የማሳጅ ባለቤቶች ከዚህ በፊት ተፈጥሮ የነበረው ችግር እመነት መሆኑን ኣምኖ ነገር ግን ለወደ ፊት የህዝቡን ባህልና እሴት በማይነካ አገልግሎት እንሰጣለን ብሎዋል።
ቀን20/03/2015ዓ.ም
ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ፀጥታ
አስተዳዳር ፅ/ቤት
Kutaa Bulchiinsaa Magaalaa Lammii kuraa waajjirri bulchiinsaa fi nageenyaa Aanaa 10 fi Buufata poolisii 30M waliin ta'uun mana Massage/Sukkummaa/ tajaajila kennanii fi jiraattootta giddutti rakkoo wal dhabdee uumamee ture irratti mari'atameera.Akka hirmattoonni wal ga'ichaa tokko tokko akka jedhanitti dogoggorri kana dura uumamee ture dhugaa ta'uu amananii,Kana booda garuu tajaajila kennan mara akka aadaa duudhaa naannicha miidhuu hin dandeenyetti hojjechuu akka qaban dubbataniiru.
Sadaasa 20/03/2015 A.l.i
Waajjira Bulchiinsaa fi Nageenya aanaa 10.
24/11/2022
በወቅታዊ ጉዳዬችን አስመልክቶ ከወረዳዉ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ተካሄደ።
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከወረዳዉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ከፖሊስ ኮምኒቲዎች ጋር ዉይይት አካሄዷል።
የወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቀነኒ ዋቅሹማ እንደገለጹት ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ችግሮች ወይም ወንጀሎች ከመፈጠራቸዉ በፊት ቅድመ መከላከል ላይ መስራት ይጠበቅብናል። ወንጀሎችና ችግሮች ከተፈጠሩም መረጃዎችን ለሚመለከተዉ አካል በፍጥነት በመስጠት የመፍትሔ አካል መሆን እንደሚጠበቅብን አክለዉ ገልጸዋል።
በዉይይቱ ላይ የተገኙት አንዳንድ ተሳታፊዎች እንደገለጹት እንደ አጠቃላይ በየአካባቢዉ ዝርፊያዎችና ስርቆቶች እንዲሁም ህገወጥ ንግዶችም ተስፋፍተዋል። በመሆኑም የሚመለከተዉ አካል በአፋጣኝ መፍትሔ ሊሰጥበት ይገባል ብለዋል።
በዉይይቱ ላይ የተገኙት የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና ሳጂን ሙሉነህ ታደሰ በሰጡት ምላሽ የሚፈጸመዉ ወንጀልና የፖሊስ ሃይል ተመጣጣኝ ባለመሆኑ በርካታ ወንጀሎች ይፈጸማሉ። ነገር ግን ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር ወይም ከፖሊስ ጋር በመሆን መከላከል እንደሚገባና የሚቀጠሩ ጥበቃዎችም ህጋዊ በሆነ መንገድ እንዲቀጠሩ በማድረግና ወንጀለኞችን ለህግ በማቅረብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የበኩሉን ድርሻ መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል።
በመጨረሻም ማንኛዉም ወንጀል የሰራ አካል ከህግ የማያመልጥ መሆኑን የወረዳዉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቀነኒ ዋቅሹማ ገልጸዋል።
ቀን15/03/2015ዓ.ም
ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ፀጥታ
አስተዳዳር ፅ/ቤት
Kutaa Bulchiinsaa Magaalaa Lammii kuraa waajjirri bulchiinsaa fi nageenyaa Aanaa 10 haalaa nageenyaa yeroo fi yakka duursanii ittisuu irratti qaamolee hawaasaa gara garaa,qaamolee nageenyaa fi poolisii wajjin iddoo hogganaan bulchiinsaa fi nageenya aanichaa,obb Qananii Waaqshumaa fi bakka bu'aan qajeelcha poolisii kutaa bulchiinsa magaalaa lammii kuraa saajiin olaanaa Mulunaa Taaddasaa waliin mari'ataniiru.
Sadaasa 15/03/2015 A.l.i
Waajjira Bulchiinsaa fi Nageenya aanaa 10.
18/11/2022
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረደ 10 ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ፅ/ቤት በቀን 09/03/2015 ዓ.ም ከወረዳው ሰላም ምክር ቤት አመራሮች እና የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች ኢንዲሁም የፅ/ቤቱ አዲሱ ሀላፊ የሆኑት አቶ ቀነኒ ዋቅሹማ ጋር የትውውቅና የቀጣይ ስራ አቅጣጫ ላይ ውይይት አድርጓል።
kutaa bulchiinsa magaalaa lammii kuraa aanaa 1o tti har'a guyyaa 09/03/2015 A.L.I tti waajjirri bulchiinsaaf nageenyaa aanichaa mana maree nageenyaa aanaa,koree dhaabbilee amantaa fi hoogganaa waajjira bulchiinsaa fi nageenyaa obb.qananii waaqshumaa waliin sirna wal baruu fi adeemsa hojimaata gara fuulduraa irratti waliin mari'ataniiru.