Bole Woreda 12 Communication

Bole Woreda 12 Communication

Share

Bole Sub City Wereda 12 Communication is a 24 hour working public media.

https://www.facebook.com/profile.php?id=100064554647803&mibextid=ZbWKwL

tiktok.com/@user9747012815681 ዘመናዊ ፣ ግልፅና ፈጣን ምላሽ መስጠት ባሀሉ ያደረገ የኮሚኒኬሽን ስርአት በመዘርጋትና በዘርፉ መሪ ሚና በመጫወት ብሎም በመንግስትና በህዝብ መካከል ጥራት ያለውን ለሁሉም ነዋሪ ተደራሽ የሆነ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ማድረግ

Photos from Bole Woreda 12 Communication's post 03/06/2026

ዛሬ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ከሆኑት ንስቲያን ክርስተንሰን ጋር ውይይት አድርገናል።

በመጪው መስከረም በኢትዮጵያ በሚካሄደው የኖርዲክ - አፍሪካ ኢቪ ሰሚት (Nordic Africa EV Summit) ላይ በጋራ በምንሰራቸው ጉዳዮች ላይ ከአምባሳደሩ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። ከተማችን አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ኩነቶችን የማስተናገድና በብቃት የመወጣት ልምድ ያካበተችና ተመራጭ እየሆነች የመጣች በመሆኗ ይህንንም ጉባኤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እናሳካዋለን።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!!

Today, we held discussions with H.E. Stian Christensen, Ambassador of Norway to Ethiopia.

We had a productive exchange with the Ambassador on areas of mutual cooperation in preparation for the upcoming Nordic Africa EV Summit, which will be held in Ethiopia this September.
During our discussion, I emphasized that our city has developed considerable experience and capacity in successfully hosting major continental and international events and is increasingly emerging as a preferred destination for such gatherings. I assured the Ambassador that, in close collaboration with all relevant stakeholders, we will organize this summit with the highest standards of professionalism and excellence.
Royal Norwegian Embassy in Addis Ababa

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

03/06/2026

የወርሀ ሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት

03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ

የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

03/06/2026
Photos from Bole Woreda 12 Communication's post 03/06/2026

በሀገር በቀል እዉቀት ፣ በህዝብ እና በመንግስት ትብብር የተገኘ ድንቅ ውጤት !

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Photos from Bole Woreda 12 Communication's post 01/06/2026

ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ድምፅ ሰጡ

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ድምፃቸውን ሰተዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

Photos from Bole Woreda 12 Communication's post 01/06/2026

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ምርጫ ጣቢያ 2 ድምፃቸውን ሰተዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

ቦሌ ኮሙኒኬሽን
ግንቦት 24/2018

Photos from Bole Woreda 12 Communication's post 01/06/2026

ኢትዮዽያ እየመረጠች ነው !
እኔም መርጫለሁ!!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Photos from Bole Woreda 12 Communication's post 01/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።

Photos from Bole Woreda 12 Communication's post 31/05/2026

በአዲስ አበባ የምርጫ ክልሎች የምርጫ የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ሥርጭት ተደራሽ በማድረግ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል

በአዲስ አበባ የሚገኙ የምርጫ ክልሎች የምርጫ የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ሥርጭት ተደራሽ በማድረግ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቅቀዋል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት 54 ሚሊየን 57 ሺህ 861 መራጮች መመዝገባቸውን አስታውቋል።

ነገ በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ማስፈጸሚያ ቁሳቁሶች በየምርጫ ጣቢያዎች በመሰራጨት ዝግጁ እየሆኑ ይገኛሉ።

በዚህም የኢዜአ ሪፖርተር በመዲናዋ በምርጫ ክልል 2 እና 14 በአካል ተዘዋውሮ እንደተመለከተው፣ በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ስርጭት ተጠናቋል።

በምርጫ ክልል 2 እና 14 ስር 14 የምርጫ ጣቢያዎች ያሉ ሲሆን የምርጫ ቁሳቁሶቹ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ተደራሽ በማድረግ ለምርጫው ሙሉ ዝግጅት መደረጉን መታዘብ ችሏል።
AMN

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address


Bole Bulbula 93 Mazoriya
Addis Ababa