23/02/2025
Best Ethiopia singer fetene
No one do anything
23/02/2025
Best Ethiopia singer fetene
15/07/2023
Same woman, same motorcycle... 71 years apart.
26/06/2023
በአምቦ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ከልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ ተልተሌ በሚባለው ቦታ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
በአምስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡
አደጋው የደረሰው ዛሬ 3፡00 ላይ ሲሆን ÷ ከአምቦ ወደ ጉደር ሰዎችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ የነበረ አነስተኛ የሕዝብ ተሸከርካሪ ከሌላ የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው ነው፡፡
15/04/2023
👉👉ዶ/ር ታዘባቸው "ትምህርቱን ከአራተኛ ዓመት እንዲቀጥል" ተወስኖለታል፡፡
ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በህክምና የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘው ዶ/ር ታዘባቸው ውዴ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማህፀንና ፅንስ ሬዚደንትነት ትምህርቱን ሲከታተል ቆይቷል፡፡
ዶ/ር ታዘባቸው ስፔሻላይዜሽን ትምህርቱን ለማጠናቀቅ ሁለት ወራት ሲቀረው በአንደኛው አይኑ ላይ ባለበት መንሸዋረር ምክንያት ትምህርቱን እንዲያቆም መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡ ወደሌላ የትምህርት ክፍል ተዘዋውሮ ከአንደኛ ዓመት እንዲጀምር መወሰኑም አይዘነጋም፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ እና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የባለሙያዎች ቡድን በማቋቋም የዶ/ር ታዘባቸውን ቅሬታ ሲመረምር ቆይቷል፡፡
የባለሙያዎች ቡድን የቀረቡለትን መረጃና ማስረጃዎች ከመረመሩና እንደገና የማጣራት ሥራ ካከናወኑ በኋላ ዶ/ር ታዘባቸው ወደ ትምህርቱ እንዲመለስ የውሳኔ ምክረ ሃሳባቸውን ለዩኒቨርሲቲው ቦርድ አቅርበዋል።
የዩኒቨርስቲው ቦርድም የባለሙያዎቹን ውሳኔ መሰረት በማድረግ ዶ/ር ታዘባቸው ትምህርቱን ከአራተኛ ዓመት እንዲቀጥል ወስኗል፡፡
ዶ/ር ታዘባቸው ትምህርቱን አቋርጦ በቆየበት ወቅት ድጋፍ ላደረጉለትና ውሳኔውን በመቃወም ለተሟገቱለት አካላት በሙሉ ምስጋና አቅርቧል፡፡
12/04/2023
እራሱን ልጅ ያሬድ እያለ የሚጠራው ወጣት በትላንትናው እለት በተፈጠረ አለመግባባት ትንሽ የአካል ጉዳት ደረሰበት!
12/04/2023
ቴሌግራም 👉 https://t.me/Merejanews
ከኮንዶሚኒየም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በ“ከባድ የሙስና ወንጀል” ከተከሰሱት ግለሰቦች ውስጥ አምስቱ በፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ!
ከአዲስ አበባ ኮንዶሚኒየም ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ በ“ከባድ የሙስና ወንጀል” ክስ ከተመሰረተባቸው ግለሰቦች ውስጥ የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያና ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱን ጨምሮ፤ አምስት ግለሰቦች በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ።
በዚሁ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ግለሰቦች መካከል አንድ ተከሳሽ በሌሉበት ጥፋተኛ ሲባሉ፤ ቀሪ አምስት ተከሳሾች ደግሞ የተከሰሱበት ድንጋጌ ተቀይሮ እንዲከላከሉ በፍርድ ቤቱ በይኗል።
ይህን ብይን የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሚያዚያ 4/2015 የዋለው፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ችሎት ነው።ችሎቱ አምስት ተከሳሾችን በነጻ ያሰናበተው፤ “ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው የሰው እና የሰነድ ማስረጃ፤ ወንጀሉን በበቂ ሁኔታ ባለማስረዳቱ” መሆኑን ገልጿል።
በነጻ ከተሰናበቱት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክ ሙያና ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ የነበሩት አብርሃም ሰርሞሎ እና የከተማይቱ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ቢሮ የአይሲቲ ዳይሬክቶሬይትን ሲመሩ የነበሩት ኩምሳ ቶላ እንደሚገኙበት ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
12/04/2023
👉👉ስንታየሁ ቸኮል በዛሬው ዕለት በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር ተፈቷል።
እንኳን ለቤትህ አበቃህ!
11/04/2023
ቴሌግራም 👉 https://t.me/Merejanews
በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የተከሰተውን የሰደድ እሳት መቆጣጠር አለመቻሉ ተገለፀ
| ከባለፈው መጋቢት 29 ቀን ጀምሮ በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የተከሰተውን የሰደድ እሳት እስካሁን መቆጣጠር አለመቻሉ ተገልጿል።
በሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኘው የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ውስጥ ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ሰደድ እሳት መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከ ቀኑ 9 ሰዓት ባልታወቀ ምክንያት መነሳቱ ተጠቁሟል።
የፓርኩ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዛናው ከፍያለው እንደተናገሩት÷ እሳቱን ለማጥፋት የአካባቢው ማህበረሰብ ቢሞክርም መቆጣጠር አለመቻሉንና ከ600 በላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እሳቱን ለማጥፋት መግባታቸውን ጠቁመዋል።
የቦታ አቀማመጡ ገደላማ መሆኑ እሳቱን ለመቆጣጠር ፈተና ሆኖብናል ያሉት ሃላፊው÷ እሳቱ ግጭ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በኩል እንደተነሳ አስታውሰዋል፡፡
ይሁን እንጂ እስከ ዛሬ ማለትም እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2015 ድረስ እሳቱ ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
በዚህም በፓርኩ የተነሳውን ሰደድ እሳት ለመቆጣጠር የሚመለከተው አካል አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረባቸውን ከዞኑ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
11/04/2023
👉👉👉ምስኪኖቹ የደቡብ ኦሞ ዜጎቻችን የእኛን እጅ ይጠብቃሉ!
11/04/2023
መምህርትና ጋዜጠኛ መስከረም አበራ ታሰረች
|
10/04/2023
📍Ensaro amhara region Ethiopia 🇪🇹
Ethiopia Land of Origins Travel to Ethiopia Visit Amhara RISE UP Hiking
10/04/2023
ቴሌግራም 👉 https://t.me/Merejanews
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን የሚከተሉትን ጥሪዎች በድጋሜ አስተላልፏል!
1. ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔያቸውን በይፋ እንዲሰርዙ ፣ ውሳኔው ስለመሰረዙ በአደባባይ እንዲገልጹ እና የአማራ ልዩ ኃይል አባላት እና የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ወደ ካምፓቻቸው እና ወደ ግዳጅ ቦታቸው እንዲመለሱ በይፋ ጥሪ እንዲያደርጉ፤
2. በፌዴራል መንግስቱ ውሳኔ እና ትዕዛዝ ከስራ ውጭ የሆኑት የአማራ ልዩ ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ፣ የብርጌድ እና የክፍለ ጦር አዛዦች ወደ ኃላፊነታቸው እና ምድብ ቦታቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ፤
3. የክልሉ መንግስት ለልዩ ኃይሉ አስፈላጊ የሆኑ የስንቅ እና ሎጂስቲክ እንዲያቀርብ እና ደሞዝ እንዲከፍል፤
4. በካምፕ እና በግዳጅ ቦታችሁ ላይ የምትገኙ ውድ የአማራ ክልል የልዩ ኃይል ፖሊስ አመራሮች እና አባላት ሠራዊቱ እንዲበተን የሚደረጉ ጥረቶችን እና የፕሮፖጋንዳ ጥቃቶችን በመቋቋም በተለመደው ሥነ-ምግባር ፣ ዲስፕሊን እና ጨዋነት የሠራዊቱን የእዝ ሰንሰለት አክብራችሁ እና ጠብቃችሁ ከህዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ፤
5. ለሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት እና አመራሮች በሙሉ በግፍ እየተጠቃ ካለው የአማራ ክልል ልዩ ኃይል እና ከአማራ ሕዝብ ጎን እንድትቆሙ እና ለግጭት ከሚጋብዙ ማናቸውም ሁኔታዎች እንድትቆጠቡ፤
6. የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የዞን እና የወረዳ አመራሮች በሙሉ በዚህ ፈታኝ ወቅት ከልዩ ኃይል ፖሊስ ሰራዊት እና ከሕዝባችሁ ጎን እንድትቆሙ፤
7. የአማራ ሕዝብ በየአካባቢው ላሉት የልዩ ኃይል አባላት አስፈላጊውን ስንቅ እና ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ድርጅታችን አብን ጥሪውን አቅርቧል።
አብን መላው የአማራ ሕዝብ እና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ከሀገር ወዳዱ የአማራ ልዩ ኃይል ጎን እንዲቆሙ ጥሪውን አቅርቧል።