A.A Housing Development & Administration Bureau

A.A Housing Development & Administration Bureau

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from A.A Housing Development & Administration Bureau, Government Organization, Addis Ababa.

02/06/2026

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡

በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡

ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡

የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ግንቦት 25 2018፣አዲስአበባ፣ኢትዮጵያ

Photos from የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ Addis Ababa City Communication's post 02/06/2026
Photos from Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ's post 01/06/2026
Photos from A.A Housing Development & Administration Bureau's post 01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
አዲስ አበባ እየመረጠች ነው!

የከተማችን ነዋሪዎች ድምፅ የመስጠት፥ ዴሞክራሲን የማፅናት ቁርጠኝነት፣ የዜግነት ድርሻ ለመወጣት ትጋት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች እየታየ ነው።

ከማለዳ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ 7ኛውን ህገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት አሁንም በአዲስ አበባ በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ቀጥሏል፡፡

Photos from A.A Housing Development & Administration Bureau's post 01/06/2026

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-

• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤

በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።

The people of Ethiopia are an extraordinary and remarkable people. Other than the Creator, who can truly know and assess our people in their entirety? Through this year’s election, Ethiopians have once again shown the world that they are a people with a rich culture, deep patriotism, and the ability to safeguard the common good.

On this historic day:

* Citizens who were not intimidated by the cold and darkness of the night,
* Who were not deterred by the midday sun or sudden rain,
* Whom weddings, funerals, childbirth, and other social obligations did not prevent from participating,
* Who were not wearied by long lines,
* Whose physical disabilities did not stop them from casting their vote,
* Those whose illness and old age did not prevent from witnessing the hope of their country,
* Who were not exhausted by carrying their infant children; the future inheritors of the nation,
* And above all, whom the shouting and threats of enemies could not intimidate or stop;

The perseverance you demonstrated amid many challenges and hardships, against all odds, was a contribution made for democracy and for the very survival of the nation. For this, you deserve heartfelt gratitude.

It is a privilege to serve such a people. Therefore, may those who have been elected honor the trust placed in them and serve this people, with integrity and sincerity! A people

Photos from A.A Housing Development & Administration Bureau's post 01/06/2026

በምሽት ተሰልፈው ለሚገኙ መራጮች ወ/ሮ መሪማ ታደሰ በነፃ ምግብና ውኃ እያቀረቡ ነው

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መሪማ ታደሰ፤ የምርጫ ቦርድ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ማራዘሙን ተከትሎ በምሽት ተሰልፈው ድምፃቸውን ለመስጠት እየተጠባበቁ ላሉ ነዋሪዎች በራሳቸው ተነሳሽነት ምግብና ውኃ በነፃ እያቀረቡ ነው፡፡

ወ/ሮ መሪማ መራጩ ሕዝብ ሳይሰለችና ሳይደክም የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ለማበረታታት ቆሎ፣ ውኃ፣ ዳቦ እና ሌሎች ቀለል ያሉ ምግቦችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡

በአሁኑ ወቅትም በክፍለ ከተማው የምርጫ ክልል 28 ሥር በሚገኙት የምርጫ ጣቢያዎች በርካታ መራጮች አሁንም ድረስ ተሰልፈው ተራቸውን እየተጠባበቁ መሆናቸው ታውቋል፡፡

Photos from A.A Housing Development & Administration Bureau's post 01/06/2026

"'ዲሞክራሲ አይገባህም፤ እኛ እናውቅልሃለን' በሚሉ ተጽዕኖዎች፣ ጉትጎታዎችንና ማስፈራሪያዎችን ሲያስተናግድ የቆየዉ ሕዝባችን፣ ዛሬ በቃል ከሚገለፀዉ በላይ ታላቅ ጽናቱን እና ለሀገሩ ያለዉን ፍቅር በተግባር አስመስክሯል።

በምርጫው ሂደት ከሌሊቱ አንስቶ በየምርጫ ጣቢያው የታየው አስደማሚ ረጅጅም ሰልፍ፣ እነሆ ምሽቱን ጭምር ተጠናክሮ በጽናት ቀጥሏል።

በዚህ ታሪካዊ የታማኝነት እና ዲምክራሲን የማፅናት ጉዞ በሕዝብ ተመርጦ የመንግሥትን በትረ ሥልጣን የሚረከብ ማንኛውም አካል፣ ይህንን ታላቅ የሕዝብ አደራ ፣ የዓላማ ጽናትና የዲሞክራሲ እምነት ከግንዛቤ በማስገባት፣ ከባድ አገራዊ ኃላፊነትን በከፍተኛ ቁርጠኝነት እንደሚቀበል እምነቴ ነው።

#ኢትዮዽያእየመረጠችነው
#ዲምክራሲ #የሕዝብሉዓላዊነት

ፈጣሪ ኢትዮዽያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address


Addis Ababa