ebro

ebro

Share

😳😏

07/03/2026

ከዚህ በላይ ምን ይመጣል ... አምስት አመት እንኳን ያልሞላው ጨቅላ በእድሜ የገፉ አዛውንት ጋር አጠገብ ላጠገብ ተረ ሽነው መንገድ ሲጣሉ ከማየት በላይ ምን ይመጣል 😢😢 ...


07/03/2026

ሰበር መረጃ

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ለማለፍ የሞከረች ነዳጅ ጫኝ መርከብ መምታቱን አስታወቀ፡፡

አብዮታዊ ዘቡ በቴሌግራም ቻናሉ አመሻሹን ባሰራጨው መረጃ "ፕሪማ" የሚል ስያሜ የነበራት ነዳጅ ጫኝ መርከብ በወሽመጡ በኩል “መተላለፍ እንደማይቻል" የተሰጠውን 'ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ' ችላ በማለቷ በድሮን መመታቷን ገልጿል።

ሰሞኑን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “አስፈለጊ ከሆነ” የአሜሪካ ባሕር ኃይል በዚያ የሚያልፉ መርከቦችን እንደሚያጅብ ተናግረው የነበረ ቢሆንም እስከአሁን ተግባራዊ ማድረግ አልቻሉም።

ለተለያዩ መረጃዎች ቤቱን ፎሎ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ እናመሰግናለን ....

04/03/2026

🇮🇱🇵🇸 ህዝቡላሃ በትናትናው ጥቃት የእስራኤል ወታደሮችን ማርኳል።
በቁጥር የማይታወቁም ሞተዋል እናም ደግሞ በጠናም የቆሰሉ አሉ። እስራኤል የቤት ስራ በዝቶበታል 😂
👇👇👇
አህመድ ሞሪንሆ

04/03/2026

🚨🚨🚨የአሜሪካ "ቢ-2" (B-2) ስቲልዝ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች በኢራን ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለመደገፍ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በእንግሊዝ በሚገኙ የጦር ሰፈሮች ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ዘ ቴሌግራፍ (The Telegraph)

03/03/2026

ሰበር ዜና፣ የኢራን መንግሥት በታሪኩ እጅግ አስቸጋሪ በሆነው የህልውና ፈተና ውስጥ ሆኖ የሥልጣን ሽግግር ለማድረግ እየታገተ መሆኑን ያሳያል። የፋርስ የዜና ወኪል (Fars News Agency) እንደዘገበው፣ የባለሙያዎች ምክር ቤት (Assembly of Experts) የአያቶላ አሊ ኻሜኒን ተተኪ ለመሰየም የመጨረሻውን ድምፅ አሰጣጥ እያከናወነ ይገኛል።

​ይህ ስብሰባ እየተካሄደ ያለው ቀደም ሲል እስራኤል በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ከተባለበት አስፈሪ ድባብ ውስጥ ሆኖ መሆኑ፣ የኢራን አመራር "አልሸነፍም" ባይነትን ለማሳየት እያደረገው ያለውን የመጨረሻ ሙከራ ያሳያል። በሌላ በኩል፣ የተገደሉት መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በሰሜን ምስራቅ ኢራን በምትገኘው መሽሃድ (Mashhad) ከተማ እንደሚፈጸም ታውቋል። መሽሃድ ለሺዓ ሙስሊሞች የተቀደሰች ስፍራ መሆኗ፣ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ሕዝባዊ ስሜትን ለመቀስቀስና ለወታደራዊ ግዳጅ አዲስ ወኔ ለመፍጠር የታለመ ስትራቴጂካዊ ውሳኔ ይመስላል።

03/03/2026
03/03/2026

🚨🚨ሰበር ዜና፦ አሜሪካ የቶማሃውክ (Tomahawk) መርከብ አጥፊ ሚሳይሎችን በኢራን ላይ ተኮሰች።

ከየካቲት 21 (Feb 28) ጀምሮ እየተካሄደ ባለውና "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊውሪ" (Operation Epic Fury) ተብሎ በተሰየመው ወታደራዊ ዘመቻ፣ የአሜሪካ ባህር ኃይል መርከቦች የቶማሃውክ (Tomahawk) ሚሳይሎችን በኢራን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ ተኩሰዋል። ሮይተርስ፣ ሲኤንኤን እና ሴንትኮም (CENTCOM) የተፈጸሙትን የአየር ድብደባዎች የሚያሳዩ ምስሎችንና ቪዲዮዎችን በማያያዝ መረጃውን አረጋግጠዋል።

Via BRICS News

Photos from ebro's post 01/03/2026

>

ከዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ሐውልት ግርጌ ላይ በፅሁፍ የተቀረፀው ዘመን የማይሽረው ድንቅ ጥቅስ ፤

ክብርና ሞገስ ከወራሪ ነፃ የሆነች ሀገር ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞቻችን 🙏💚💛❤️

#አድዋ

01/03/2026

ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ወራሪዎችን ሲታገሉ ኖረዋል

። ። ። ። ። ። ። ። ። ። ። ። ።
ኢራን ታላቁ አያቶላህ ኢማም ሰይድ አሊ ኻሚኒ ማለፋቸውን ገልፃለች

86 አመታትን ሲኖሩ ህይወታቸውን በትግል አብዮታዊነት እና ስኬት አሳልፈዋል ።

ኢራንን ከአሜሪካ እና ኢስራኤል ተላላኪ መንግስት አላቀው በኢራን እምነት እና ማንነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ኢስላማዊ መንግስት መስርተው መርተዋል።

ጭቆናን የሚታገሉትን ጨቋኞችን ሳይፈሩ አግዘዋል።

ታላቁ አያቶላህ ኢማም ሰይድ አሊ ኻሚኒ አልፈዋል የሚለው ዜና ለአለም ሰላም እና ፍትህ ለሃገራት ሉዐላዊነት የሚታገሉትን ሁሉ አሳዝኗል።

አያቶላህ አሊ ኻሚኒ 86 ዓመታቸው ሲሆን በሁለንተናዊ መሪነት አገራቸውን ማገልገል የጀመሩት ከፈረንጆቹ 1989 አንስቶ ነበር።

የእስላማዊት ኢራን መስራችን እና የመጀመሪያውን አያቶላህ ሩሆላህ ሆሚኒን ተከተው ነው ወደ መሪነቱ የመጡት።

የ1979ኙን የኢራን አብዮት ተከትሎ የሻህ አስተዳደር ከቴህራን ፖለቲካ ተባሮ መቀመጫውን አሜሪካ በማድረግ በመግለጫ እየኖረ ይገኛል ።

አያቶላህ አሊ ኻሚኒ የአገሪቱን ጦር፣የመንግስት ከፍተኛውን አሰተዳደር እና የመንፈሳዊ መሪነቱንሚና ሲወጡ የነበሩ ታላቅ መሪ ናቸው።

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Website

Address


Addis Ababa
Addis Ababa
1000