Yeka Woreda 08 Communication - የካ ወረዳ 08 ኮሙንኬሽን

Yeka Woreda 08 Communication - የካ ወረዳ 08 ኮሙንኬሽን

Share

➭ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በዚህ ፔጅ ያግኙ!
➭Get current and accurate information on this page.

Photos from Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ's post 02/06/2026
Photos from Yeka Woreda 08 Communication - የካ ወረዳ 08 ኮሙንኬሽን's post 02/06/2026

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-

• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤

በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።

The people of Ethiopia are an extraordinary and remarkable people. Other than the Creator, who can truly know and assess our people in their entirety? Through this year’s election, Ethiopians have once again shown the world that they are a people with a rich culture, deep patriotism, and the ability to safeguard the common good.

On this historic day:

* Citizens who were not intimidated by the cold and darkness of the night,
* Who were not deterred by the midday sun or sudden rain,
* Whom weddings, funerals, childbirth, and other social obligations did not prevent from participating,
* Who were not wearied by long lines,
* Whose physical disabilities did not stop them from casting their vote,
* Those whose illness and old age did not prevent from witnessing the hope of their country,
* Who were not exhausted by carrying their infant children; the future inheritors of the nation,
* And above all, whom the shouting and threats of enemies could not intimidate or stop;

The perseverance you demonstrated amid many challenges and hardships, against all odds, was a contribution made for democracy and for the very survival of the nation. For this, you deserve heartfelt gratitude.

It is a privilege to serve such a people. Therefore, may those who have been elected honor the trust placed in them and serve this people, with integrity and sincerity! A people who have paid a great price for the democratic system. May you be worthy of that responsibility.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Photos from Yeka Woreda 08 Communication - የካ ወረዳ 08 ኮሙንኬሽን's post 01/06/2026

በምሽት ተሰልፈው ለሚገኙ መራጮች ወ/ሮ መሪማ ታደሰ በነፃ ምግብና ውኃ እያቀረቡ ነው

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መሪማ ታደሰ፤ የምርጫ ቦርድ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ማራዘሙን ተከትሎ በምሽት ተሰልፈው ድምፃቸውን ለመስጠት እየተጠባበቁ ላሉ ነዋሪዎች በራሳቸው ተነሳሽነት ምግብና ውኃ በነፃ እያቀረቡ ነው፡፡

ወ/ሮ መሪማ መራጩ ሕዝብ ሳይሰለችና ሳይደክም የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ለማበረታታት ቆሎ፣ ውኃ፣ ዳቦ እና ሌሎች ቀለል ያሉ ምግቦችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡

በአሁኑ ወቅትም በክፍለ ከተማው የምርጫ ክልል 28 ሥር በሚገኙት የምርጫ ጣቢያዎች በርካታ መራጮች አሁንም ድረስ ተሰልፈው ተራቸውን እየተጠባበቁ መሆናቸው ታውቋል፡፡

Photos from የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ Addis Ababa City Communication's post 01/06/2026
01/06/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ 12:00 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እንደሚቀጥል ያሳውቃል።

ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።

Photos from Yeka Woreda 08 Communication - የካ ወረዳ 08 ኮሙንኬሽን's post 01/06/2026

የኢትዮጵያን መፃዒ እድል ለመወሰን ወሳኝ የሆነዉ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት አንደቀጠለ ነዉ፡፡

የኢትዮጵያን መፃዒ እድል ለመወሰን ወሳኝ የሆነዉ ይህ ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳዉ 12 ሰዓት የተጀመረዉ 7ኛዉ ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምቸዉን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

01/06/2026

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ነው - የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

AMN - ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።

ምክር ቤቱ ይህንን የገለጸው በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በተቋቋመውና የምርጫ ሂደቱን በቀጥታ በሚከታተልበት የክትትል ክፍል በሰጠው መግለጫ ነው።

በመግለጫው፤ መራጩ ሕዝብ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲሰፍን ከፍተኛ ጨዋነት በተሞላበት መልኩ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ከቤቱ በመውጣት ድምፅ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሶ ለዚህም ምስጋና አቅርቧል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሐሳባቸውንና ርዕዮተ-ዓለማቸውን በመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት ካስተዋወቁ በኋላ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ለመራጭነት መመዝገቡን ያስታወሰው ምክር ቤቱ፣ ዛሬ እስከ እኩለ ቀን ባለው ሂደትም ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ መዋሉን ገልጿል።

ምክር ቤቱ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ባለው መዋቅር አማካኝነት መረጃዎችን ሲለዋወጥና ሂደቱን ሲከታተል እንደነበር የጠቆመ ሲሆን፤ እስካሁን ባለው ሂደት የጸጥታ አካላት፣ ታዛቢዎች እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች እያደረጉ ባለው ገለልተኛ አገልግሎት መደሰቱንም አስታውቋል።

በቀሪው የድምፅ አሰጣጥ ሂደትም ህዝቡ እስካሁን ባለው ጨዋነትና ትዕግሥት የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጋራ ምክር ቤቱ ጥሪውን አቅርቧል።

01/06/2026
Photos from Yeka Woreda 08 Communication - የካ ወረዳ 08 ኮሙንኬሽን's post 01/06/2026

የኢፌዴሪ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ምርጫ መሐንዲስ ኮንዶሚንዬም ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

Photos from Yeka Woreda 08 Communication - የካ ወረዳ 08 ኮሙንኬሽን's post 01/06/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አለምፀሀይ ጳውሎስ ድምፃቸውን ሰተዋል።

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Telephone

Address


Addis Ababa