Covid19 Response Ministerial Committee Secretariat - Ethiopia

Covid19 Response Ministerial Committee Secretariat - Ethiopia

Share

Official page of the Ethiopian COVID19 Response Ministerial Committee Secretariat

20/09/2020
18/09/2020

07/09/2020

#ምክንያትአልሆንም

07/09/2020

ተጨማሪ 1 ሺህ 206 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው የ21 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 25 ሺህ 158 የላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 206 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 58 ሺህ 672 ደርሷል።

በሌላ መልኩ በትናንትናው ዕለት 531 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በአገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 21 ሺህ 307 ሆኗል።

ባለፉት 24 ሰዓታት የ21 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን በአጠቃላይ በኮሮናቫይረስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 918 ደርሷል።

በአሁኑ ወቅት 36 ሺህ 445 ቫይረሱ ያለባቸው ሲሆን 308 ሰዎች ደግሞ በጽኑ ሕክምና ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካዛሬ ድረስ 1 ሚሊዮን 44 ሺህ 5 የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል።

Photos from Ministry of Health,Ethiopia's post 30/08/2020
Deputy Premier, Health Minister visit COVID 19 field hospital 29/08/2020

Deputy Premier, Health Minister visit COVID 19 field hospital Addis Ababa, August 29, 2020 (FBC) –Deputy Prime Minister Demeke Mekonnen and Minister of Health Dr Lia Tadesse today visited a field hospital being prepared to receive COVID-10 patients.Located in Addis Ababa at Bole Bulbula, the hospital was built

18/08/2020

ልጆች የቡሄ በዓልን በቤት ወስጥ አንዲያከብሩ በማድረግ የኮሮና ቫይረስ በሽታን ይከላልከሉ

#ምክንያትአልሆንም

15/08/2020

ከኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያ በተለቀቁ ሐሰተኛ መረጃዎች የተነሳ 800 ሰዎች ህይወታቸዉን አጥተዋል፡ ጥናት

አዲስ አበባ ነሃሴ 7/2012፡ በፈረንጆቹ 2020 የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ በተለቀቁ የተሳሳቱ መረጃዎች ምክንያት በዓለም ዙሪያ ቢያንስ 800 ሰዎች መሞታቸውን ተመራማሪዎች ገልፀዋል፡፡

በአሜሪካ ጆርናል ኦፍ ትሮፒካል ሜዲካል እና ሃይጂን ላይ የታተመ ጥናት እንዳመለከተው በማህበራዊ ሚዲያዎች በተሰራጩ የሐሰት መረጃዎች ምክንያት 5,800 የሚሆኑ ሰዎች ወደ ሆስፒታል መግባታቸውን ገልጿል፡፡

በጥናቱ እንደተገለፀው ለሞት የተዳረጉት ሰዎች በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጩ ሐሰተኛ መረጃዎችን በመቀበል ሲሆን አንዳንዶቹ ሜታኖልን በመጠጣት አልያም ከአልኮል ጋር የተያያዙ የጽዳት ምርቶችን እንደተጠቀሙም ታዉቋል፡፡

ለአደጋዉ ተገላጭ ከሆኑት ሰዎች መካከል በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጩ ሐሰተኛ መረጃዎች መሠረት ምርቶቹ ከቫይረሱ ፈዋሽ እንደሆኑ በስህተት አምነዉ የተጠቀሙ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በዚህም ሳቢያ አጭበርባሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጩትን መረጃዎች አስታከዉ የራሳቸወዉን ጥቅም እንዲያጋብሱ እንዳስቻለቸው ጥናቱ አመልክቷል፡፡

የቫይረሱን ለመከላከል የሚያስችሉ ክትባቶች በሚወጡበት ጊዜም ፀረ-ክትባት ዘመቻዎችን በመክፈት ሰዎች ራሳቸውን ከቫይረሱ እንዳይጠብቁ ለማሳመን የማህበራዊ ሚዲያ መድረክን ይጠቀማሉ የሚል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን መረጃዉ አመልክቷል፡፡

አሁን ላይ ምንም እንኳን የማህበራዊ ሚዲያ ኩባንያዎች ስለ ክትባቶች አሳሳች መረጃዎችን በማስወገድ እና የማስተካከያ እርምጃዎች እየወሰዱ ቢሆንም ተፈላጊዉ ለዉጥ አለመምጣጡን መረጃዎች ያሳያሉ ሲል ቢቢሲ በድረ-ገጹ አስነብቧል፡፡

በሀገራችንም በስፋት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ እየታዩ ያሉ መዘናጋቶች ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈለ ይገኛል፡፡ ምንጭ፡ ቢቢሲ

15/08/2020

ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ!

የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን የመከላከል ሥራችን ተጠናክሮ እንዲቀጥል፣ በዓለም የጤና ድርጅት የተጀመረውን የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛን የሚያስተዋውቅ ዘመቻ ሀገራችን “ማስክ ኢትዮጵያ” በሚል ተቀላቅላለች::
በዚህ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ዘመቻ የሁላችንም ተሳትፎ ጨምሮ፣ እውቀታችን አድጎ፣ ባህሪአችንም ተለውጦ፣ ወረርሽኙን በተሻለ አቅም መከላከል እንችላለን ብዬ አምናለሁ፡፡

ሁላችንም፣ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛን በብዛት በማምረት፣ በትክክል በማድረግ፣ እባካችሁ ራሳችንንም፣ ወገኖቻችንንም ከበሽታ እንጠብቅ!

አንድም ሰው በበሽታ እንዲያዝ ፣ የማይተካ ሕይወት እንዲያልፍ ፣ የአገራችን እድገት እንዲስተጏጎል ምክንያት አንሁን!!

የሁላችንም ያልተቋረጠና የተባበረ ጥረት ወረርሽኙን ለማሸነፍ ይሁን!

My fellow Ethiopians,

has launched the challenge to promote the use of face masks in fighting the spread of . Ethiopia has followed suite by launching .

Let us all take part in this campaign by promoting the proper use of face masks as we all work to put a stop to this pandemic.

Wearing masks saves lives!

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮሮና ያደርሳል ተብሎ ከተተነበየው አስከፊ ጉዳት ታድጎናል - አቶ ደመቀ መኮንን - Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C 13/08/2020

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮሮና ያደርሳል ተብሎ ከተተነበየው አስከፊ ጉዳት ታድጎናል - አቶ ደመቀ መኮንን - Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 7 ፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የኮሮና ቫይረስ ያደርሳል ተብሎ ከተተነበየው አስከፊ ጉዳት ታድጎናል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ተናገሩ። የ...

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Address


Ethio-Chinese Friendship Road
Addis Ababa
5608

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00