07/03/2026
ዜና እረፍት
========
የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የስራ ባልደረባ የነበረችው ሳጅን ፅዩን አበበ ከአባቷ አቶ አበበ ይማም ከእናቷ ከወ/ሮ ፍሬህይወት ደምሴ በሐረር ከተማ በአባድር ወረዳ ቀበሌ 05 በ1986 ዓ/ም ተወለደች።
አባሏ በፖሊስነት ለማገልገል ባላት ፍላጎት ሰኔ 1/2008 በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን በፖሊስነት ተቀጥራ ስታገለግል ቆይታለች አባሏ ከኮንስታብል እስከ ሳጅን ማእረግ የደረሰች ሲሆን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል ለ10 አመታት በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የድንገተኛና እሳት አደጋ መከላከል ክፍል አገልግላለች ።
አባሏ በደረሰባት የጤና እክል ምክንያት ህክምና እየተከታተለች ብትቆይም ሊሻላት ባለመቻሉ የካቲት 27/2018 ዓ/ም በተወለደች በ32 አመቷ ከዚህ አለም ድካም አርፋለች ቀብሯም በሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።
አባሏ በሒይወት በነበረችበት ግዜ 3 ልጆች ያፈራች ሲሆን የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል ዳሬክቶሬት በአባሏ ህልፈተ ሒይወት የተሰማዉን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለወዳጅ ዘመዶቿ መፅናናትን ይመኛል።

07/09/2023
07/09/2023