20/05/2024
#ኢራን
ኢራን በሂሊኮፕተር አደጋ በሞቱት በኢብራሂም ራይሲ ሞትክ ፕሬዝዳንት ሾመች!
የኢራን ምክትል ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ሞክበር አዲሱ የኢራን ፕሬዝዳንት ተደርገው መመረጣቸው ተሰምቷል፡፡
የኢራን ከፍተኛ መሪ ዓሊ ኮማኒ ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ የሚገኙትን ሞክበርን በሄሊኮፕተር አደጋ በሞቱት ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ ምትክ ሾመዋቸዋል፡፡
ኮማኒ ሹመቱን ያስታወቁት በፕሬዝዳንት ራይሲ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ለመግለጽ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት ነው፡፡
08/03/2022
በካርኪቭ አቅራቢያ በተካሄደ ጦርነት የሩሲያ ጦር ከፍተኛ አዛዥ መገደላቸውን የዩክሬን ጦር የስለላ አገልግሎት አስታወቀ።
ቢቢሲ ጉዳዩን ከገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ ያልቻለ ሲሆን የሩሲያ ባለስልጣናትም በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት አልሰጡም።
የዩክሬን መከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መሠረት ቪታሊ ጌራሲሞቭ፤የሜጀር ጄኔራል ማዕረፍ ያላቸው ሲሆንየ41ኛው የሩሲያ ማዕከላዊ ዕዝ ምክትል ዋና አዛዥ ነበሩ።
በርካታ ከፍተኛ የሩሲያ የጦር መኮንኖችም መገደላቸውን እና ቀሪዎቹም መቁሰላቸውን ገልጿል ይሄው የዩክሬን ተቋም።
የዩክሬን የስለላ ድርጅት እንዳስታወቀው ጌራሲሞቭ በሁለተኛው የቺቺን ጦርነት እና በሶሪያ የሩሲያ ወታደራዊ ዘመቻ ወቅት መሳተፋቸውን ገልጿል። "ክራይሚያን ለመመለስ" ባደረጉት አስተዋጽኦም ሜዳልያ አግኝተዋል።
የዩክሬን ባለስልጣናት የጌራሲሞቭ ነው ያሉትን ፎቶ በትዊተር ይፋ ያደረጉ ሲሆን “ተወግዷል” የሚለው ቃል ከስሩ በቀይ ቀለም አስፍረዋል።
22/10/2021
የሱዳን ሽግግር መንግሥት ደጋፊዎች ወደ ካርቱም ጎዳናዎች ሲተሙ ተቃዋሚዎች ደግሞ ወታደራዊ መንግሥትን በመደገፍ በቤት የመቀመት አድማ አድርገዋል።
በወታደራዊ እና በሲቪል መሪዎች መካከል ያለው ከፍተኛ መከፋፈል ወደ ዴሞክራሲ የሚደረገውን ሽግግር ሊያደናቅፈው ይችላል ተብሏል።
ለረዥም ጊዜ በፕሬዝዳንት ያገለገሉት ኦማር አልበሽር እአአ በ2019 ከስልጣን ከተነሱ ማግስት ስልጣን ለመጋራት ተስማምተው ነበር።
በመስከረም ወር በአልበሽር ተከታዮች ተደረገ ከተባለው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ከተከሸፈ በኋላ ውጥረቱ አይሏል።
መከፋፈሉ የቀድሞውን ፕሬዝዳንት ለማስወገድ ያገዘውን የነጻነትና የለውጥ ኃይሎች በተባለው ስብስብ መካከል እንዲከፋፈል ምክንያት ሆኗል።
ሐሙስ ዕለት የሲቪሉን መንግሥት የሚደግፉ አንቂዎች ጎማ ሲያቃጥሉ እና የሱዳን ባንዲራን ሲያውለብልቡ የፀጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ ተኩሰዋል።
17/10/2021
የሱዳን ወደ ዴሞክራሲ መሸጋገርን የሚቃወሙ ዜጎች ሠራዊቱ የአገሪቱን የሥልጣን መንበር እንዲቆጣጠር ቅዳሜ ዕለት ጎዳና ወጥተው ጠየቁ።
የአገሪቱ የፖለቲካ ቀውስ እየተባባሰ በመጣበት በዚህ ወቅት በበርካታ ሺህ የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ከፕሬዚዳንቱ ቤተ መንግሥት ውጪ ተሰብስበው ነበር።
እአአ በ2019 ፕሬዝዳንት ኦማር አልባሽር ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ ወታደራዊ እና ሲቪል ቡድኖች ስልጣን ተጋርተው የሽግግር መንግሥት አዋቅረው ነበር።
ይሁን እንጂ ባለፈው መስከረም ወር ላይ የአልባሽር ተከታዮች እንደተካሄደ ከተገለጸው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ መክሸፍ በኋላ ውጥረቱ አይሏል።
08/04/2021
የአውሮፓ መድኃኒት ተቆጣጣሪ መስሪያ ቤት ለኮቪድ-19 መከላከል አስትራዜኒካ ክትባትን የሚወስዱ ሰዎች በደም መርጋት የመጠቃታቸው እድል እጅጉን አናሳ ነው ሲል ገለፀ።
በአውሮፓ የተከሰቱ በርካታ የደም መርጋቶችን የመረመረው የአውሮፓ መድኃኒቶች ኤጀንሲ፣ ክትባቱ ከሚያስከትለው ጉዳት ይልቅ ጥቅሙ የላቀ ነው ሲል ተናግሯል።
አስትራዜኒካን የወሰዱ ሰዎች በቀጥታ በደም መርጋት ይጠቃሉ የሚለውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ፍንጭ አላገኘሁም ያለው ኤጀንሲው፤ አብዛኞቹ የተመዘገቡት ክስተቶች እድሜያቸው ከ60 በታች በሆኑ ሴቶች ላይ ሲሆን የተወሰኑ ወንዶችም ችግሩ ገጥሟቸዋል ሲል አብራርቷል።
ኤጀንሲው 86 የደም መርጋት የገጠማቸውን ህሙማን ጉዳይ መርምሯል።
የአውሮፓ ሕብረት ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን የአስትራዜኒካ ክትባት መውሰዳቸው ተገልጿል።
08/04/2021
ለንደን የሚገኙት የምያንማር አምባሳደር ወደ ኤምባሲው ቅጥር ግቢ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ገለፁ።
አምባሳደሩ ኪያው ዝዋር ሚን እምዳሉት የምያንማር ወታደራዊ አታሼ የኤምባሲውን ሠራተኞች ቢሯቸውን ለቅቀው እንዲወጡ ካደረገ በኋላ እሳቸውንም ከአሁን በኋላ የአገሪቷ ወኪል አለመሆናቸውን ገልጾላቸዋል።
አምባሳደሩ ለሮይተርስ የዜና ወኪል " ከግቢው አስወጥተው ቆልፈውብኛል" ብለዋል።
የምያንማር ወታደራዊ ኃይል በመፈንቅለ መንግሥት ስልጣን የያዘው በፈረንጆቹ የካቲት 1/2021 የነበረ ሲሆን ይህም ለሳምንታት የዘለቀ ተቃውሞና አመጽ አስከትሏል።
24/03/2021
ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ቴክኖሎጂውን በመጠቀም ሙከራ እንደተደረገና በቅርቡ በይፋ እንደሚገለጽ ተናግረዋል።
ከሕዝብ ቁጥር እና የእርሻ መሬት ፍላጎት መጨመር ጋር በተያያዘ ደረቅ አካባቢዎችን ለምና ምርታማ ለማድረግ ቴክኖሎጂው እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።
17/02/2021
ከህዝብ እይታ ተሰውረው የነበሩት የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ባለቤት ከአመት በኋላ መታየታቸውን የአገሪቱ ሚዲያ ዘግቧል።
በያዝነው ሳምንት ማክሰኞ በባለቤታቸው አባትና የቀድሞ መሪ የልደት መታሰቢያን በማስመልከት በተዘጋጀ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ታይተዋል ተብሏል።
ከዚህ ቀደም ትልልቅ ዝግጅቶች ላይ መሪው ባለቤታቸውን አጅበው የሚገኙት ቀዳማዊት እመቤት ሪ ሶ ል ጁ ለየት ባለ ሁኔታ ለአንድ አመት ያህል ከህዝብ እይታ ጠፍተው ነበር።
ለዚህም መጥፋታቸው አንዳንድ መላምቶች የተሰጡ ሲሆን ከጤና እክል ጋር በተያያዘ እንዲሁም ነፍሰ ጡር ሊሆኑ ይችላሉ የሚሉ ነበር።
የሰሜን ኮሪያ ብሔራዊ ደህንነት አገልግሎት በበኩሉ በትናነትናው ዕለት ለምክር ቤቱ እንዳሳወቀው ሪ ሶ ልጁ ከህዝብ እይታ የጠፉት ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ጋር በተያያዘና እንዲሁም ከልጆቻቸው ጋር አብረው ለማሳለፍ በመምረጣቸው ነው ብሏል።
እስካሁን ባለው መረጃ ሰሜን ኮሪያ አንድም በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው አላገኘሁም ትላለች። አንዳንድ ባለሙያዎች ግን ይህንን ሃሳብ አይቀበሉትም።
ሮዶንግ ሲንመን ዘገባ መሰረት በትናንትናው እለት ባለትዳሮቹ ማንሱዴ አርት ቲያትር ሲገቡ በርካቶች በጭብጨባ እንደተቀበሏቸው ነው።
ከቦታው የወጡ ፎቶዎች እንደሚያሳዩት ሲጫወቱና ሲስቁ ሲሆን፤ ጭምብል አላጠለቁም እንዲሁም አካላዊ ርቀታቸውን አልጠበቁም ተብሏል።
ሪ ሶል ጁ ማን ናቸው?
ቀዳማዊት እመቤት ሪ ሶል ጁ አባቷ በሙያቸው ፕሮፌሰር ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ የህክምና ዶክተር ናቸው።
አስተዳደጋቸው ከላይኛው መደብ የሚመደቡና፤ ሃብታም ናቸው።
የ31 አመቷ ሪ ሶል ጁ ከዚህ ቀደም ኡንሃሱ በሚባል ኦርኬስትራ ውስጥ ዘፋኝ ነበሩ።
ከመሪው ኪም ጋር የተጋቡት በአውሮፓውያኑ 2009 ሲሆን ይህም የቀድሞው መሪና የኪም አባት በጠና ታመው እያለ በአጣዳፊ ያቀዱት ነው ተብሏል።
ምንም እንኳን ከተጋቡ አመታትን ቢያስቆጥሩም የኪም ባለቤት መሆናቸው የታወቀው የአገሪቱ ሚዲያዎች ይፋዊ በሆነ መንገድ ባለቤት ብለው መጥራት ከጀመሩ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ነው።
የደቡብ ኮሪያ ደህንነት በበኩሉ ባለትዳሮቹ ሶስት ልጆች እንዳላቸው ይፋ አድርጓል።
01/02/2021
ኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ክትባትን በመጪው ሚያዚያ ወር ወደ አገር ውስት እንደምታስገባ ገለጸች።
የሚገባው የኮሮናቫይረስ መከላከያ ክትባት ቢያንስ 20 ከመቶ ለሚሆኑ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚዳረስ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ይህንን የክትባት ሥራ የሚያስተባብር ግብረሃይል በብሄራዊ ደረጃ መቋቋሙም ተገልጿል።
20/01/2021
በያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት በወታደራዊ ኃይል ጥንካሬ ዝርዝር ውስጥ ከገቡት የአፍሪካ አገራት መካከል ኢትዮጵያ የስድስተኛነትን ቦታ ስትይዝ በዓለም 60ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣላች።
06/01/2021
በተወለዱ በጥቂት ቀናት ውስጥ ይሞታሉ ተብለው ሲጠበቁ የነበሩት የተጣበቁ መንትዮች በሕይወት ኖረው ከአራት ዓመት በኋላ ወደ ትምህርት ቤት መሄዳቸው ተሰምቷል።