01/06/2026
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ 12:00 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እንደሚቀጥል ያሳውቃል።
ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።
01/06/2026
የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒክማ ከይረዲን በሀላባ ቁ.1 ምርጫ ክልል ለሀገራችን ይበጃል ያሉትን ፓርቲ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
01/06/2026
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ሰጡ
****************
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በሀዲያ ዞን ሶሮ 01 የምርጫ ክልል በጊምቢቹ ከተማ አስተዳደር 01 ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ሀዲያ #
01/06/2026
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
ምርጫ በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ ዜጎች የፖለቲካ ፈቃዳቸውን የሚገልጹበት እና የሀገራቸውን መፃኢ ዕጣ የሚወሰኑበት ወሳኝ ሂደት ነው።
ዜጎች ያላቸውን የመራጭነት መብት በንቃት ሲጠቀሙበት ጥቅሙ ለመላው ሕዝብና ለሀገር እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ አይቀሬ ነው።
የምርጫ ዕድልን መጠቀም የዜግነት ኃላፊነትንም ያጎለብታል።
መራጮች የምርጫ እድላቸውን መጠቀማቸው የሕዝብ ድምፅ እንዲሰማ፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲጠናከር ብሎም የሀገር ልማት በሕዝብ ፍላጎት መሠረት እንዲመራ ያደርጋል።
ዜጎች ያላቸውን የመራጭነት መብት በኃላፊነት በመጠቀም የወደፊት ዕድልን ለመገንባት ጠቅላላ ምርጫው ወሳኝ ሚና አለው።
01/06/2026
የኢትዮጲያ እናቶች እየመረጡ ሀገር እያጸኑ ነው!!!
01/06/2026
የምጥ ህመም ያልበገርዉ ዲሞክራሲን የማፅናት ጉዞ!
ኢትዮጲያ እየመረጠች ነዉ!
በዛሬው ዕለት የወለደችው እናት ተገላግላ በሀለት ሰዓታት ልዩነት ድምጿን በመስጠት ህዝባችን ለዴምክራሲ ግንባታ ያለዉን ቁርጠኝነት አስመስክራለች።
የመቱ ከተማ ነዋሪ የሆነችው መምህርት ኮኬብ ተመስገን ወልዳ በተገላገለች በሁለት ሰዓት ውስጥ በቢሻሪ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጿን ሰጥታለች። ይህ ለአገርና ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያላትን የላቀ እምነት ያሳየችው እናት፥ በዕለቱ የተወለደችውን ልጇንም "ምርጫ" ስትል ሰይማታለች።
ይህ ተግባር ዜጎች ለዲሞክራሲያዊ መብታቸውና ለሀገራዊ ጥሪያቸው ያላቸውን ጥልቅ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ትልቅ አርአያነት ያለው ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል።
01/06/2026
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ድምፅ ሰጥተዋል።
01/06/2026
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
የክልል ርዕሳኔ መስተዳድሮች ድምፅ ሰጥተዋል።