ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office

ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office, Government Organization, Addis Ababa.

እንኳን ወደ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ በደህና መጡ!

ይህ ገፅ በክፍለ ከተማችን የሚከናወኑ የጽ/ቤቱ ተግበሰራት እና ተያያዥ አገልግሎቶችን በተመለከተ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን ለነዋሪው ተደራሽ ለማድረግ የተዘጋጀ ነው።

12/04/2026
Photos from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office's post 04/04/2026

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷ ደግሞ ብቁ የማድረግ ትልቅ ግብ የሰነቀ ነው። የከተማ አስተዳደሩ "ልማቱ ሰውን ማዕከል ያደረገ መሆን አለበት" በሚል በያዘው አቋም መሠረት በኮሪደሩ ዳርቻ የፈረሱ የንግድ ቦታዎችን ለመተካት በዘመናዊ መልኩ የተገነቡ ሱቆችን ለተነሺዎች ቅድሚያ በመስጠት የማስተላለፍ ስራ በከፍተኛ ትኩረት እየተከናወነ ይገኛል።የአዲሳ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 የተገነቡ በኮሪደር ልማት የለሙ ሱቆችን ለልማት ተነሺዎች በዕጣ የማስተላለፍ መረሃ ግብር አከናዉኗል።

Photos from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office's post 30/03/2026

የዛሬውን ወርቃማው ሰኞ ምክንያት በማድረግ በቦሌ ክፍለ ከተማ የቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት የመንግስት ሰራተኞች መብቱን እና ግዴታውን አውቆ ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎት መስጠት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ የልምድ እና አውቀት ሽግግር ተካሄደ።
ይህ የውይይት መድረክ በዋናነት የመንግስት ሰራተኛውን መብትና ግዴታ በዝርዝር ከመረዳት ባለፈ፣ በጽህፈት ቤቱ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ለነዋሪው ምቹ ለማድረግ ያለመ ነው።

Photos from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office's post 28/03/2026

የአረንጓዴ አሻራን በዘላቂነት ማጽናት፦ የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በወረዳ 12 የእንክብካቤ ስራ አከናዉኗል።
የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት አመራርና ባለሙያዎች በ2017 የክረምት ወቅት የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በዛሬው ዕለት በወረዳ 12 አካባቢ በስኬት አከናውነዋል። በንቅናቄው ላይ የጽ/ቤቱ የስራ መሪዎችና መላው ሰራተኞች በነቃ ተሳትፎ የተገኙ ሲሆን። በመድረኩ የተገኙ የስራ ኃላፊዎች እንደተናገሩት፡- ችግኝ መትከል ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የተከልነውን አጽድቆ ለትውልድ ማሳለፍ የሁላችንም ኃላፊነት ነው ብሎዋል። ይህም የከተማዋን ውበት ከመጠበቅ ባለፈ ለነዋሪዎች ምቹ አየር እንዲኖር ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።

Photos from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office's post 23/03/2026

የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር በየሳምንቱ ሰኞ የሚያካሂደው "ወርቃማ ሰኞ" የውይይት መድረክ ዛሬም በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል። የዛሬው የውይይት መሪ ቃል "አገልግሎት እና ስነምግባር" የሚል ሲሆን፣ በጽሕፈት ቤቱ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ ቁልፍ ነጥቦች ላይ የእውቀት ሽግግር ተከናውኗል።

Photos from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office's post 16/03/2026

በቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽሕፈት ቤት በየሳምንቱ ሰኞ ጠዋት የሚከናወነው የ**"ወርቃማ ሰኞ"** መርሐ-ግብር ዛሬም በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

የዛሬው የውይይት ትኩረት "የተግባቦት (Communication) ጽንሰ-ሀሳብና አስፈላጊነት" በሚል ርዕስ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ በሥራ አካባቢ ሊኖር ስለሚገባው ጤናማ የመረጃ ልውውጥ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የማዳመጥ ጥበብ፦ የደንበኞችን ፍላጎትና ቅሬታ በትዕግሥት ማዳመጥ ለችግሮች ግማሽ መልስ ነው።
የጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች በውይይቱ ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን፣ የተገኘውን ግንዛቤ ወደ ተግባር በመቀየር ለክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ግልጽነት የተሞላበትና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ብሏል።

Photos from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office's post 10/03/2026

በቀን 30/06/2018 ዓ.ም "አመለካከት ለሁሉም ነገር ወሳኝ ነው"፦ በሚል ማሪ ቃል በቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር የእውቀት ሽግግርና የውይይት መድረክ ተካሄደ
የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት የሰራተኞችን ክህሎት ለማሳደግና ተገልጋይን ማእከል ያደረገ አሰራርን ለማጠናከር ዘዎትር ሰኞ የሚካሄደው "ወርቃማ ሰኞ" “Attitude is Everything” (አመለካከት ለሁሉም ነገር ወሳኝ ነው) በሚል መሪ ቃል ውይይትና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ። የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ይህንን "ወርቃማ ሰኞ"ን የመማማሪያ መድረክ በማድረግ፣ ሰራተኛው በዕውቀት ብቻ ሳይሆን በስነ-ልቦናም ተዘጋጅቶ ህዝቡን እንዲያገለግል እና መልካም ልምዶቻቸውን በማካፈል የስራ መነቃቃት እና ተነሳሽነት የሚፈጥሩበት ነው፡፡

Photos from ቦሌ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት/Bole Sub City Housing Dev. & Admin Office's post 28/02/2026

የስድስት ወር የግምገማ ግብረመልስን መነሻ በማድረግ የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ውይይት ዋና ዋና ነጥቦች እና በታዩ ጥንካሬዎች እና መስተካከል በሚገባቸው ጉድለቶች ላይ የጋራ መግባባት ላይ የተደረሰ እና ውይይቱ የሚያሳየው ካለፉት ስድስት ወራት ክፍተት በመማር፣ ለቀጣዩ ግማሽ ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከፍተኛ ተነሳሽነት መኖሩን ነው።

Photos from A.A Housing Development & Administration Bureau's post 28/11/2025
Photos from ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን Addis Ababa Housing Development Corporation's post 06/11/2025
02/11/2025

ማስታወቂያ

ከ7ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ
👇👇👇👇👇👇👇

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address


Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30