Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር

Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር

Share

The Ministry of Peace established to prevent and resolve conflicts, to bring equitable development among the regions and to create stable nation.

The Ministry of Peace was established under proclamation number 1097/2011 on October 16, 2018. The office of the Ministry of Peace was created to sustain the reforms that Ethiopia is currently undergoing through peace-building measures, establishing, and strengthening the rule of law, and building the capacity of peace and security focused sectors. Additionally, the office is tasked with using alr

Photos from Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር's post 04/06/2026

የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ

ግንቦት 27/2018 ዓ.ም(የሰላም ሚኒስቴር)፤ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በውጭ ግንኙነት መምሪያ ሊቀ መንበር ብፁዕ አቡነ አንቶኒ ሴቭሪዩክ የተመራውን የልዑካን ቡድን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ መሀመድ እድሪስ በሁለቱ ሀገራት፣ ህዝቦች እና አብያተ ክርስቲያናት መካከል ዘመናትን ያስቆጠረ እንዲሁም ልዩ የሆነ ሰላማዊ አብሮነትን ያጎላ ለዓለም ምሳሌ የሆነ
የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን ይህም በትብብር ለመስራት የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑን በአፅንኦት ገልፀዋል።

የቮሎኮላምስክ ሜትሮፖሊታን እና የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሞስኮ ፓትርያርክ የውጭ ግንኙነት መምሪያ ሊቀ መንበር የሆኑት ብፁዕ አንቶኒ ሴቭሪዩክ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በተደጋጋሚ ወደ ተጠቀሰችው ታሪካዊት ሀገር ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ በመምጣታቸው ጥልቅ የሆነ ደስታ እና ክብር እንደተሰማቸው ገልጸው በሩሲያ እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት መካከል ያለው ግንኙነት ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ መሆኑን አመላክተው፤ በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም በሀገራቱ መካከል ለሚኖረው ታላቅ የወደፊት ተስፋ ማረጋገጫ መሆኑን ተናግረዋል።

በውይይቱ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ /ር ከይሬዲን ተዘራ፣ በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ ከፍተኛ አማካሪ አቶ አሌክሴ ቼስኖኮቭ፣ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የውጭ ግንኙነት መምሪያ የክርስቲያናዊ ግንኙነት ጉዳዮች ጸሐፊ ሂሮሞንክ ስቴፋን፣ የብፁዕ አቡነ አንቶኒ የግል ረዳት ቄስ አሌክሳንደር ኤርሾቭ፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና የደቡብ ኦሞ እና አሪ ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሊቃውንት ጉባዔ አባል እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌስር ቀሲስ መምህር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ተገኝተዋል።

Honorable Mr. Mohammed Idris, the Minister of the Ministry of Peace, received the delegation of the Russian Orthodox Church at his office and had discussions.

June 4/2026 (Ministry of Peace): The Minister of Peace, Honorable Mr. Mohammed Idris, received in his office the delegation led by the Chairman of the Department of External Church Relations of the Moscow Patriarchate of the Russian Orthodox Church, His Holiness Mr. Anton Sevryuk.

During their meeting, Honorable Mr. Mohammed Idris emphasized that the two countries, people, and churches have a close relationship that has been going on for centuries and that emphasizes a unique peaceful coexistence that is an example to the world, and that this is of great importance for working together.

The Metropolitan of Volokolamsk and the Chairman of the Department of External Church Relations of the Moscow Patriarchate of the Russian Orthodox Church, his Holiness Anton Sevryuk, expressed his deep joy and honor in coming to the historical country of Ethiopia, which is frequently mentioned in the scriptures, for the first time. His Holiness pointed out that the relationship between the Russian and Ethiopian Orthodox Churches has been going on for a long time and said it is proof of the great future between the two churches and countries.

State Minister for Peace Building and National Consunsus at the Ministry of Peace, Dr. Keiredin Tezera; Senior Counselor of the Russian Embassy in Ethiopia, Mr. Aleksei Chesnokov; Secretary for Inter-Christian Relations of the Department of Foreign Relations of the Russian Orthodox Church, Hiromonk Stefan; Personal Assistant of the Chairman of Metropolitan Anthony, Priest Aleksandr Ershov; President of Holy Trinity Theological University and Archbishop of South Omo and Ari Zone Diocese, His Holiness Abune philipos as well as the member of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church and the teacher and researcher of the Holy Trinity Spiritual University, Assistant Professor Daniel Seife Michael, were present at the discussion.

04/06/2026

አንድ ቀላል መልዕክት ምን ሊቀይር ይችላል?

ሰላም ለኢትዮጵያችን!
-
How much can one simple message change?

Peace for our Ethiopia!

04/06/2026

🤝 መደጋገፍ
🤝 ባህልን እና ልዩነትን ማክበር
🤝 ሰብዓዊ መብቶችን እውቅና መስጠት
🤝 ማኅበራዊ ሀብቶችን መጠበቅ እና መንከባከብ የአብሮነት መሠረቶች ናቸው።

አብሮነት ከሌለ የሚሳካ የጋራ ርዕይ እና ግብ አይኖርም፤ ሰላሟ የተጠበቀ እና ጠንካራ ሀገር ለመገንባት አብሮነት ወሳኝ ነው።

🔑 ለልማት
🔑 ለሀገር ሰላም
🔑 ለማኅበራዊ ትስስር
🔑 ችግሮችን በጋራ ለመወጣት እና የጋራ ደህንነትን ለማረጋገጥ አብሮነት እጅግ አስፈላጊ ነው።

ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

#የሰላምሚኒስቴር #ትብብር #አስተሳሳሪእሴቶቻችን #ብዝሃነት #ሰላም #ኢትዮጵያ

04/06/2026

አንድነታችን በእጃችን! 🕊️

ሰላም ለኢትዮጵያ! 🇪🇹
-
Our Unity in Our Hands! 🕊️

Peace for Ethiopia! 🇪🇹

#የሰላምሚኒስቴር #ሰላም #ሰላማዊነት #ሰላምግንባታ #ኢትዮጵያ #አብሮነት #አንድነት

03/06/2026

ሰላም ለኢትዮጵያችን!
Peace for our Ethiopia!

#ሰላምግንባታ #ሰላማዊነት #ሰላም #ኢትዮጵያ #

03/06/2026

ሀገራዊ አንድነትን እና ብሔራዊ መግባባትን የሚያጎለብቱ የባህል ልውውጥ ሥራዎችን እንደሚያከናውን የሰላም ሚኒስቴር ከተሰጡት ተልዕኮዎች መካከል ነው።

ተቋማችን ይህን ተልዕኮ ለመወጣት ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ “በጎነት ለአብሮነት” በሚል መሪ ሐሳብ ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ ፕሮግራም በመንደፍ በርካታ ወጣቶችን እያሳተፈ ይገኛል።

⚠️ የሰላም በጎ ፈቃድ ፕሮግራም በታሪክ ሂደት ውስጥ የተፈጠሩ እና የተዛነፉ ትርክቶችን ለማስተካከል የተቀረፀ ፕሮግራም ነው።

ፕሮግራሙ በዋናነት ወጣቶች ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የሚገኙ ወጣቶችን በመመልመል፣ በዩኒቨርስቲዎች በማስልጠን እና በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በማሰማራት ወጣቶች ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን እንዲያጎለብቱ የሚያደርግ ነው።

ኢትዮጵያዊ እሴቶችን እና መርሆችን ለወጣቱ ትውልድ በማስተላለፍ በዘር፣ በጎሳ፣ በሃይማኖት እና ሌሎች ማንነቶችን መሠረት አድርጎ ያለው ልዩነት ጌጥ እንጅ ዕዳ አለመሆኑን በመገንዘብ ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ ያተኮረ ጠንካራ ሀገርን ለመገንባት ታስቦ እየተሠራበት ያለ ፍሬያማ ፕሮግራም ነው።

ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

#አብሮነት

03/06/2026

ሰላማችን በእጃችን! 🕊️

ሰላም ለኢትዮጵያ! 🇪🇹
-
Our Peace in Our Hands! 🕊️

Peace for Ethiopia! 🇪🇹

#የሰላምሚኒስቴር

02/06/2026


ምላሽዎን በኮሜንት ያሳውቁን! 👇
ሰላም ለኢትዮጵያችን! ‌‌

Let us know your answer in the comments! 👇
Peace for our Ethiopia! ‌‌

#ሰላምግንባታ #ሰላማዊነት #ሰላም #ኢትዮጵያ #

02/06/2026

ከእኛ ምን እየተማሩ ነው?
ሰላም ለኢትዮጵያችን!
-
What are they learning from us?
Peace for Our Ethiopia!

#አብሮነት #ሰላም

02/06/2026

የረጅም ዘመን ታሪክ ያላት ሀገራችን ኢትዮጵያ ሕዝቦቿ ለበርካታ ዓመታት ተሳስበው፣ ተከባብረው እና ተደጋግፈው የኖሩባት ሀገር ናት።

በሀገራችን ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ እሴቶቻችን ሰላማችንን በመጠበቅ እና ግጭቶችን በመፍታት ረገድ ቁልፍ ሚና ሲጫወቱ ኖረዋል።

እነዚህ እሴቶች፡-
📌 በችግር ጊዜ ደራሽ
📌 በደስታ ጊዜ አጋዥ
📌 በሃዘን ጊዜ አጽናኝ እና
📌 በግጭት ወቅት ደግሞ አስታራቂ ህዝብን ሲያፈሩ ቆይተዋል።

ግጭቶች ሲፈጠሩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዳችን በፊት በባህላዊ የእርቅ ሥርዓቶቻችን መፍትሔ የማግኘት ልምዳችን የሚደነቅ ነው።

እነዚህን የቆዩ የሰላም ግንባታ ጥበቦቻችንን ለዛሬው ትውልድ ማስተላለፍ እና በዘመናዊ አሠራር ውስጥ እንዲካተቱ ማድረግ ለዘላቂ ሰላማችን ዋስትና ነው።

ሰላም ለኢትዮጵያ! 🕊

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

https://www.tiktok.com/@ministryofpeaceethiopia, https://www.youtube.com/@ministryofpeace1263, h

Address


Ethio-Chinese Friendship Road
Addis Ababa
5608

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30