ኢዜማ - አዲስ አበባ ምርጫ ወረዳ 20/Ezema - Addis Abeba Woreda 20

ኢዜማ - አዲስ አበባ ምርጫ ወረዳ 20/Ezema - Addis Abeba Woreda 20

Share

የዜግነት ፖለቲካ
ማሕበራዊ ፍትህ
ዴሞክራሲያዊ ፌደራሊዝም
ሰላማዊነት
ትብብር
ውይይት ጉዞ ወደሰለጠነ የዜግነት ፖለቲካ!

23/03/2026

“ኢዜማ የብሔር ፌዴራሊዝም አወቃቀርን በመተው ዜጎች በእኩልነት የሚኖሩባትን ሀገር ለመገንባት ይሠራል”

- አቶ ኢዮብ መሳፍንት
የኢዜማ ፓርቲ መሪ
++++++++++++++++++++++++++++

#ጋዜጣ ፕላስ | ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት የብሔር ፌዴራሊዝም አወቃቀር ወጥታ ዜጎች በእኩልነት የሚኖሩባትንና የጋራ ባለቤትነታቸው የሚረጋገጥባትን ሀገር ለመገንባት እንደሚሠራ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ ገለጸ፡፡

የፓርቲው መሪ አቶ ኢዮብ መሳፍንት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም የሀገሪቱ ግዛት እኩል የመኖርና የባለቤትነት መብት ያለው እንጅ በየትኛውም ቦታ አንዱ ከሌላው የተለየ ልዩ መብት ሊኖረው አይገባም፡፡

ኢዜማ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አሸንፎ ስልጣን ቢይዝ ክልሎች የማንነት፣ የልማት አመቺነት፣ የአስተዳደር ምቹነት እና ኢኮኖሚያዊ ራስን መቻልን መሰረት ባደረጉ 4 መስፈርቶች ይዋቀራሉ፡፡

ይህ አዲሱ የክልሎች አወቃቀር አሁን ካለው አሠራር ጋር ሙሉ ለሙሉ ልዩነት ያለው መሆኑንና ለሁሉም ዜጎች እኩል የባለቤትነት መብት እንደሚሰጥም አቶ ኢዮብ መሳፍንት አስታውቀዋል።

ኢዜማ በምርጫ ማኒፌስቶውም ሆነ በፖሊሲ አማራጮቹ የዜግነት ፖለቲካ ያራምዳል ያሉት የፓርቲው መሪ፤ ሁሉም የባለቤትነት ጥያቄ የሚነሳባቸው "አከራካሪ" ቦታዎች እና የሀገሪቱ ክልሎች የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ንብረት ናቸው ብሎ ያምናል ብለዋል፡፡

የወሰን ክርክሮችና “የእኔ ግዛት” የሚሉ ትርክቶች ለሀገራዊ አንድነትና ሉዓላዊነት ከፍተኛ ስጋት መሆናቸውን የተናገሩት አቶ ኢዮብ፤ “በዚህ ክልል አንተ መጤ ነህ፣ እኔ ባለቤት ነኝ” የሚሉ ኋላ ቀር አመለካከቶች በአስቸኳይ ሊቆሙ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የባለቤትነት ስሜት መሸርሸር ዜጎች ሀብታቸውን አፍስሰው እንዳይሰሩና የሀገር ሉዓላዊነትን ለመጠበቅ እና ከውጭ ወራሪ ለመከላከል ያላቸውን ተነሳሽነት እንደሚቀንስ የጠቆሙት አቶ ኢዮብ፤ ይህ አይነቱ አካሄድ እንዲታረም ፓርቲያቸው እንደሚሠራ አስታውቀዋል።

በመዓዛ ማሞ
+++++++++++++++++++++
@ጋዜጣ-ፕላስ #ኢትዮጵያ #ኢዜማ #ምርጫ #ፖለቲካ #7ተኛው #ሀገራዊምርጫ

22/03/2026

ስለጎዳና ማናዬ የምናውቀውን ብቻ ከምንነግራችሁ:

እናንተ የገፃችን ተከታታዮች ኢንጂነር ጎዳና ማናዬ እንዴት ትገልፁታላችሁ?

አስተያየቶቻችሁ:

በግለሰቡ የፖለቲካ ትግል ላይ ቢያውጠነጥኑ መልካም ነው።

እኛ ከምንነግራች የተሻለ እናንተ ትመሰክሩለታላችሁ እና

በዞናችን የብሔር የጎሳ እና የዘውግ ፖለቲካ ላይ ያላለሰለሰ ትግሉን በመጥቀስ:

የዓላማ ፅናቱን ለተተኪው ትውልድ በመዘርዘር:

የወደፊት ህልሙን በመረዳት ስለባስኬቶ ያነገበውን መልካም ራዕይ በመጥቀስ:

በቀጣይ ዞናችንን ወክሎ በምክር ቤት የሚያደርገውን ትግል ከግምት በማስገባት አስተያየቶቻችሁን ስጡን:

የእናንተን ሀሳብ እና የኛን መረጃዎች አጠናቅረን የጎሰኞች መድሃኒት ስለሆነው ኢንጂነር ጎዳና ማናዬ የምናውቀውን እንመሰክራለን!
⚖️

22/03/2026
22/03/2026
22/03/2026

ዜጎች በእጃቸው በያዙት የምርጫ ካርድ ሊመራቸው የሚገባውን ይመርጣሉ!
⚖️
በአንድ ሀገር ውስጥ የተለያየ ዓይነት የአስተዳደር ፍላጎት እና ጥያቄ ሊኖር ይችላል። ይህንን ፍላጎታቸውን የሚገልጡት በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ፍላጎታቸውን ያሳውቃሉ። ከምርጫ ጣቢያቸው በሚያገኙት የምርጫ ካርድ ይህንን መብታቸውን ለሚተማመኑበት ዕጩ ይሰጣሉ።

ኢዜማ 1258 እናንተ የምትተማመኑባቸውን ዕጩዎችን አቅርቧል። ከእነዚህ ውስጥ 299 የፓርላማ ተወካዮች ከመረጣችሁ በኢትዮጵያ ላይ በ275 ተወካዮች የሚደራጅ ለዜጎች ቅድሚያ የሚሰጥ ስርዓተ መንግስት ያደራጃሉ።

እንደባስኬቶ ዞን ለኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት ብርቱ እና ጠንካራ ዕጩዎችንና ሰባት ለደቡብ ኢትዮጵያ እልል ምክር ቤት ዕጩዎችን አስመዝግበናል።

በየምርጫ ክልላችሁ ተገኝታችሁ ከሚቀርባችሁ የምርጫ ጣቢያ ካርድ በመቀበል የትኛውን ዓይነት አስተዳደር እንደሚፈልጉ ያሳውቁ። ይወስኑ።

እንጂነር ካሣሁን ወንድወሰን ምናሴ
የኢዜማ ባስኬቶ ዞን ሰብሳቢ

22/03/2026

የ #ኢዜማ ሴት አመራሮች "ቅድሚያ ለሴቶች" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የሳፋሪኮም 5KM ሩጫ ላይ..

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ

09/02/2026

!

በምርጫ ብቻ መንግሥት ለመሆን እየሞከርን ነው!!

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ

09/02/2026

!

ኑሮህን ያከበደብህን ሙሰኝነት በአማራጭ ሐሣብ ለመለወጥ፤ እየሞከርን ነው!!

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ

09/02/2026

ኢዜማ በምርጫ ብቻ ወደ ሥልጣን ለመምጣት ''እየሞከርኩኝ ነው'' አለ

| የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በመጪው የ2018 ዓ.ም አገራዊ ምርጫ ላይ በንቃት እንደሚሳተፍና በምርጫ ብቻ መንግሥት ለመሆን ''እየሞከረ'' መሆኑን አስታውቋል።

ፓርቲው ባስተላለፈው መልዕክት፣ የሥልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጠው በሕዝብ ነፃ ምርጫ ብቻ መሆን እንዳለበት ያለውን ጽኑ እምነት ዳግም አረጋግጧል። "እየሞከርን ነው" በሚል መሪ ቃል ፓርቲው እያከናወነ ያለውን የቅስቀሳና የዝግጅት ሥራዎች ያመለከተ ሲሆን፣ ይህም በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲገነባና ሰላማዊ ምርጫ እንዲኖር ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመልክቷል።

የ2018 ዓ.ም ምርጫ የኢትዮጵያን የወደፊት የፖለቲካ አቅጣጫ ለመወሰን ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ኢዜማም ለዚህ ታሪካዊ ኹነት ራሱን እያዘጋጀ መሆኑን ገልጿል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

#ጌጡ
#ኢዜማ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ዴሞክራሲ #የምርጫቅስቀሳ #ሰላማዊትኢትዮጵያ

Photos from የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ - ኢዜማ Ethiopian Citizens for Social Justice's post 01/02/2026
01/02/2026

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው መሠረት የመራጮች ዲጂታል ምዝገባ የሚከናወንባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር
✍️

ላስካ መደበኛ የምርጫ ክልል ውስጥ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች

1, ሆስፒታል ሰፈር
2, ላስካ ዶንኪ ዕድር አዳራሽ መንደር
3, አንድነት ዕድር አዳራሽ ፊት ለፊት
4, አዲሱ ገበያ መንደር
5, ኦቾ ወንዝ መንደር
6, ቡንባሳ ባስኬቶ ጤና ኬላ መንደር
7, ቡንባሳ ወላይታ ግብርና ጽ/ቤት መንደር
8, አንግላ ቁጥር 1 የወጣቶች መዝናኛ መንደር
9, አንግላ ቁጥር 2 ጤና ጣቢያ
10, አንግላ ቁጥር 3 ጤና ጣቢያ
11, አንግላ ቁጥር 4 ግብርና ጽ/ቤት
12, ለምለም ንዑስ ት/ቤት መንደር
13, ጋራ ሃዲያ መንደር
14, ጋራ ወላይታ ግብርና ጽ/ቤት

ባስኬቶ ልዩ የምርጫ ክልል ውስጥ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች

1, ቃይሻ የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን መንደር
2, ጋንችሬ ቃይሻ መካነ ኢየሱስ ዕድር አዳራሽ
3, ሉታ ኔትወርክ መንደር
4, ኤላ የወጣቶች መዝናኛ
5, ዛባ ግብርና ጽ/ቤት
6, ሞትከሳ መንደር
7, ሜንዲታ ጤና ኬላ መንደር
8, ሚዝጋዋ ግብርና ጽ/ቤት
9, አርዛቃ ግብርና ጽ/ቤት
10, ሣሣ ማኬሳ ገበሬዎች ማሰልጠኛ መንደር
11, ሣሣ ማኬሳ ግብርና ጽ/ቤት
12, ሼላ ካንቦላ ቱልትላ መንደር
13, ሼላ ካንቦላ ጮጪጋርታ መንደር
14, ሻንካ ጋምጋይላ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት መንደር
15, ባዮ ቦራዝ ግብርና ጽ/ቤት
16, ባዮ ቦራዛ ጤና ኬላ መንደር
17, ቦላ ባስኬቶ አርብ ገበያ መንደር
18, ቦላ ጋባላ ግብርና ጽ/ቤት
19, ቦላ ጋባላ ጤና ኬላ መንደር
20, ቦናሬ ማርቃና ጤና ኬላ መንደር
21, ቦኩ ቡጫ የመምህራን መጠለያ መንደር
22, ሶስታ ት/ቤት መንደር
23, አውራ መንደር
24, ዳልባ ጤና ጣቢያ መንደር
25, ኦብጫ አዲሱ ገበያ መንደር
26, ኦብጫ ግንባ ጤና ጣቢያ መንደር
27, ሱባ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት መንደር
28, ዋጳ ጤና ጣቢያ መንደር
29, ዶኮ ኣይማ ገበያ መንደር
30, ዶኮ ከተማ ገበሬዎች ማሠልጠኛ መንደር
31, ጋቲጋልዳ መንደር
32, ዳብፃ ዳልቅንሳ ጫጫላ መንደር
33, ጋርባያ ጤና ኬላ መንደር
34, ጌዛ ኣይማ ት/ቤት
35, ጋራ ባስኬቶ ግብርና ጽ/ቤት
36, ግምጳ ሙርማሻ ጤና ኬላ መንደር

በየሰፈራችሁ በመሄድ የምርጫ ካርድ መውሰድ ትችላላችሁ!

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Category

Telephone

Website

Address


Addis Ababa