በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም C/E Worabe Prison Institution

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution

Share

የህግ ታራሚዎችን አርሞና አንፆ አምራች ዜጋ ሆነው ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረግ።

29/03/2025

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው ኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን የወራቤ ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ኮማንደር አወል ሁሴን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፤ በማረሚያ ተቋማት ለሚገኙ የፓሊስ አባላት፤ሲቪል ሠራተኞች እና የህግ ታራሚዎች በሙሉ እንኳን ለ1446 ኛው ኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የእስልምና እምነት ተከታዮች በዓሉን ሲያከብሩ እርስ በእርሱ በመደጋገፍ እና በመተባበር አብሮነትን በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ኮማንደሩ ተናግረዋል።

የኢድ አል ፈጥር በዓል ሲከብር የተቸገሩ ወገኖችን በማብላት፤በማጠጣት የተለመደ የመተዛዘንና የመረዳዳት ባህሉን ፍቅሩን በማዳበር እንዲሁም የህግ ታራሚዎች በመጠየቅ በመተሳሰብ ማክበር እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 29/03/2025

የስልጤ ዞን መጅሊስ በወራቤ ማረሚያ ተቋም በእርምት ላይ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ለኢድ አል ፈጥር በዓል መዋያ የአስቤዛ መግዣ የብር ድጋፍ አደረገ ።

መጋቢት 20/2017 ዓ/ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በወራቤ ማረሚያ ተቋም በእርምት ላይ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች የኢድ አል ፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ የስልጤ ዞን መጅሊስ ለበዓል መዋያ የአስቤዛ መግዣ የአርባ ሰባት ሺ ብር /47000 / አበርክቷል፡፡

የብር ድጋፉን የተረከቡት የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ባስተላለፉት መልዕክት በበዓል ወቅት ያለውን ተካፍሎ ማሳለፍ ኢትዮጵያዊ ባህላችን ከመሆኑም በላይ በእርምት ላይ የሚገኙ የሕግ ታራሚዎችን መጠየቅ በእምነቱም በፈጣሪ ዘንድ ከፍተኛ አጅር ምንዳ የሚያሰጥ ተግባር ነው ብለዋል፡፡

በስልጤ ዞን መጅሊስ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ውስጥ ሆነው የኢድ አል ፈጥር በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ የዞኑ መጅሊስ ያደረገው የበዓል መዋያ የብር ድጋፍ ለማረም ማነፅ ስራው ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው ገልፀዋል፡፡

የህግ ታራሚ ሽማግሌዎች ድጋፉን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት በስልጤ ዞን መጅሊስ ለተደረገላቸው ድጋፍ በህግ ታራሚዎች ስም ምስጋናቸውን በማቅረብ ለኸይር ስራቸው አላህ እንዲመነዳቸው ዱሃ አድርገዋል።

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 26/03/2025

ከወራቤ ማረሚያ ተቋም 126 የሕግ ታራሚዎች 1ሺ 446ኛዉን የዒድ አልፈጥር እና መጪዉን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ የይቅርታ መስፈርት አሟልተው የተገኙ የህግ ታራሚዎች በክልሉ መንግሥት ውሳኔ በይቅርታ ተፈቱ።

መጋቢት 17/2017 ዓ.ም

የወራቤ ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ኮማንደር አወል ሁሴን እንደተናገሩት በወንጀል ጉዳይ እስራት ተፈርዶባቸው በወራቤ ማረሚያ ተቋም በመታረም ላይ ከሚገኙት 968 የህግ ታራሚዎች ውስጥ ህጉ የሚጠይቀውን መመዘኛ አሟልተው ለተገኙ በመደበኛ ወንድ 123 ሴት 3 በድምሩ 126 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ እንደተደረገላቸው ገልጸዋል፡፡

የወራቤ ማረሚያ ተቋም ተራሚዎችን ከማረምና ከማነጽ ባሻገር በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ባለቤት በመሆን አምራች ዜጋ እንዲሆኑ በማድረግ ወደ ማህበረሰባቸው እንዲቀላቀሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ሲያከናውን መቆየቱንም አንስተዋል።

የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ኑረዲን ሀምዳላ እና የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ክትትል ዳይሬክቶሬት አቶ ሬድዋን ኑሪ የሕግ ታራሚዎቹ በይቅርታ ሲፈቱ በወራቤ ማረሚያ ተቋም ተገኝተው የይቅርታዉ ተጠቃሚዎች በሚኖሩበት ማህበረሰብ ዉስጥ ሲቀላቀሉ በመልካም ስነምግባራቸው ዓርዓያ በመሆን ህብረተሰቡን እንዲክሱ የንቃተ ህግ ትምህርት እና ምክር በመስጠት መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል በሰጡት አስተያየት በቆይታ ጊዜያቸውም የህግ የተለያዩ የምክር አገልግሎት ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

ባገኙትም ግንዛቤ በተገቢው ከወንጀል ርቀው ለማህበረሰባቸው መልካም ዕሴትን ለማስተማር ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።

በማዕከላዊ ክልል መንግስት ውሳኔ ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ-ታራሚዎች በማረሚያ ቆይታቸው ወቅት በቂ ትምህርት የተሰጣቸውና በፈፀሙት የወንጀል ድርጊት ተፀፅተው የታነጹ ስለመሆናቸው በየደረጃው በመረጋገጡ ፤ አንዳንዶቹም እርቅ ስለመፈጸማቸውና የገንዘብ መቀጮ ያለባቸውም ገንዘቡን ስለመክፈላቸው ስለተረጋገጠ ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርግላችው ተጠይቋል ።

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 23/03/2025

የስልጤ ዞን አስተዳደር በወራቤ ማረሚያ ተቋም በእርምት ላይ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ለኢድ አል ፈጥር በዓል መዋያ የ1 ሰንጋ በሬ ድጋፍ / ሰደቃ/ አበረከተ ።

መጋቢት 14/2017 ዓ/ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በወራቤ ማረሚያ ተቋም በእርምት ላይ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ለመጪው የኢድ አል ፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ የስልጤ ዞን አስተዳደር ለበዓል መዋያ የሚሆን ሰንጋ በሬ አበርክቷል፡፡

ድጋፉን የተረከቡት የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ባስተላለፉት መልዕክት በበዓል ወቅት ያለውን ተካፍሎ ማሳለፍ ኢትዮጵያዊ ባህላችን ከመሆኑም በላይ በእርምት ላይ የሚገኙ የሕግ ታራሚዎችን መጠየቅ በእምነቱም በፈጣሪ ዘንድ ከፍተኛ አጅር ምንዳ የሚያሰጥ ተግባር ነው ብለዋል፡፡

በስልጤ ዞን አስተዳደር ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ውስጥ ሆነው የኢድ አል ፈጥር በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ የዞኑ አስተዳደር ያደረገው የበዓል መዋያ ሰንጋ ድጋፍ ለማረም ማነፅ ስራው ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው ገልፀዋል፡፡

የህግ ታራሚዎች ተወካይ የሆነው አህመድ ቢላል ና የህግ ታራሚ ሽማግሌዎች ድጋፉን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት በስልጤ ዞን አስተዳደር ለተደረገላቸው ድጋፍ በህግ ታራሚዎች ስም ምስጋናቸውን በማቅረብ ለኸይር ስራቸው አላህ እንዲመነዳቸው ዱሃ አድርገዋል።

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 17/03/2025

ከረመዳን ወር ኢባዳዎች መካከል የታመመን፣ የታሰረን፣ለየቲሞችና ለሚስኪኖች ሰደቃ ማድረግና ማስፈጠር አንዱ የእምነቱ ተግባር ነው።

መጋቢት 8/2017 ዓ/ም

መቀመጫውን አዲስ አበበ ላይ ያደረገው ነጃሺ ኢሮፖ ዲቪሎፕመንት ቪዠን በእህታችን ፍጢማ ስራጅ /ፋጤ/ አማካይነት በወራቤ ማረሚያ ተቋም በእርምት ላይ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ለረመዳን ወር ማፍጠሪያ የሚሆን ግምቱ ዘጠና ሺህ ብር የሚያወጣ /90,000/ የበሬና የቴምር ሰደቃ አደረገ ።

በህግ ታራሚ ሽማግሌዎችም ለተደረገው ሰደቃ አላህ በማያልቀው ኒሂማው አጥፍ ድርብ አድርጎ እንዲመነዳቸው ዱሃ ተደርጎላቸዋል ።

የተቋሙ ሀላፊ ኮማንደር አወል ሁሴን በነጃሺ ኢሮፖ ዲቪሎፕመንት ቪዠን በእህታችን ፍጢማ ስራጅ /ፋጤ/ አማካይነት ለህግ ታራሚዎች ለተደረገላቸው የረመዳን ወር ፆም ማፍጠሪያ ሰደቃ ወይም ድጋፍ በህግ ታራሚዎች ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን በማቅረብ ሌሎች አለል ከይሮችም የህግ ታራሚዎች በማስታወስ የሀጅሩ ተካፍይ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 22/02/2025

ታራሚዎችን በመልካም ስነ-ምግባር እንዲታነጹ ከማድረግ ባለፈ አካላዊና ስነ-ልቦናዊ አቅማቸዉን ለማዳበር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የወራቤ ማረሚያ ገለጸ!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
የወራቤ ማረሚያ ተቋም ላለፉት ሳምንታት የእግር ኳስ ዉድድሮችን በተለያዩ ምድቦች ሲያካሄድ መቆየቱን ገልጿል።

በዕረፍት ቀናቶች መርሃ-ግብር ላለፉት 16 ሳምንታት ሲከናወን የቆየዉ የተቋሙ የቤት ለቤት የእግር ኳስ ዉድድር በዛሬዉ ዕለት ፍጻሜዉን አግኝቷል።

በፍጻሜውም ❝8 ቁጥር እግር ኳስ ቡድን❞ “2 ቁጥር እግር ኳስ ቡድንን” በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል።

በዋንጫ ፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ኃላፊ ኮማንደር አወል ሁሴን እንደተናገሩት የህግ ታራሚዎችን በስነ-ምግባር ከማነጽ ባለፈ አካላዊና ስነ-ልቦናዊ አቅማቸዉን ለማጎልበት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አብዱል ፈታ ሱልጣንን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በፕሮግራሙ ተገኝተዋል።

በመጨረሻም ለተለያዩ አካላት የተለያዩ ሰርተፍኬት እና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ሲል የዘገበው የወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን ነው።

ለሁለቱም ቡድኖች የስፖርት ትጥቁን ያበረከተው የስልጤ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ መሆኑ የሚታወስ ነው።

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 14/02/2025

ፍሰሐ እሸቱ (ዶ/ር ) የተከሰሱበት የሙስና ወንጀል ክስ እንዲቋረጥ የተሰጠው ብይን ተሻረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፐርTዝ ብላክ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሐ እሸቱ (ዶ/ር) የተከሰሱበት የሙስና ወንጀል ክስ በሌሉበት መታየት አይቻልም ተብሎ ክሱ እንዲቋረጥ በስር ፍርድ ቤት የተሰጠው ብይን በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 1ኛ ይግባኝ ሰሚ ወንጀል ችሎት ተሻረ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ የፐርTዝ ብላክ ኢቲኤች ትሬዲንግ አ/ማ የቦርድ አባልና ዋና ስራ አስፈጻሚ እነ ፍሰሐ እሸቱ (ዶ/ር) ጨምሮ በ10 ግለሰቦች ላይ እና በሁለት ድርጅቶች ላይ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከባድ ማታለል የሙስና ወንጀል ተደራራቢ ክስ አቅርቦባቸው እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል።

ዐቃቤ ሕግ በአዲስ አበባ ከተማ 100 ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ ባለ 3 መኝታ ቤት መኖሪያ ቤት በ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚሸጥ መሆኑን በሚዲያ በማስተዋወቅ ሰዎች ቤት ለመግዛት በሄዱበት ጊዜ ላይ "መጀመሪያ ገንዘቡን አስገቡና ውሉን ትመለከታላችሁ" በማለት ከሌሎች ግብረዓበሮቻቸው ጋር በመሆን አሳሳች ቃላቶችን በመጠቀም፣ ሰዎች ገንዘቡን ካስገቡ በኋላ ደግሞ የአክሲዮን ግዢ ውል እንዲፈርሙ በማድረግ ምንም አይነት የግንባታ ቦታ ባልተረከቡበት ሁኔታ 2 ቢሊየን 234 ሚሊየን 200 ሺህ ብር በመሰብሰብ ቤቱን ሰርተው ሳያስረክቡ በመቅረት እንዲሁም ግማሹን ገንዘብ ወደ ውጭ እንዲሸሽ በማድረግ፣ ኮሚሽን በመቀበልና በማታለል የወንጀል ድርጊት ተፈጽሟል በሚል ነበር ክስ ያቀረበው።

ክስ ከቀረበባቸው ተከሳሾች መካከል ተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሱት ፍሰሃ እሸቱ (ዶ/ር) በቀረበባቸው ስድስት ተደራራቢ ክስ መሰረት በተደጋጋሚ ችሎት ያልቀረቡ መሆኑን ተከትሎ የስር ፍርድ ቤቱ ጉዳያቸው በሌሉበት መታየት አይችልም በማለት ክሱ እንዲቋረጥ ብይን ሰጥቶ ነበር።

በስር ፍርድ ቤት በአብላጫ ድምጽ የተሰጠው ብይን አግባብ አደለም በማለት ዐቃቤ ሕግ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 1ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ይግባኝ ብሏል

ችሎቱ የዐቃቤ ሕግ ይግባኝ እና የመልስ ሰጪ የስር ፍርድ ቤቱን ብይን መርምሮ ውሳኔ ሰጥቷል።

በዚህም የወ/መ/ስ/ስ/ህ/ቁጥር 161 ንዑስ ቁጥር 2 (ሀ) ሊተረጎም የሚገባዉ በክሱ የተጠቀሰው ድንጋጌ ላይ የተመላከተዉ ቅጣት ወደ 12 አመት ጽኑ እስራት የሚቀርበዉ መነሻ ቅጣቱ ነዉ ወይስ መድረሻ (ጣሪያ) ቅጣት ነዉ የሚለዉ እየተመዘነ መሆን እንዳለበት በስ/መ/ቁ 231732 ከተሰጠዉ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ይዘት ለመገንዘብ የሚቻል መሆኑን ጠቅሷል።

ፍስሐ እሸቱ (ዶ/ር) የተከሰሱባቸዉ ክሶች ከ5ኛ ክስ ዉጪ ያሉት ወንጀሎች የሚያስቀጡት ከ12 አመት እና ከዛ በላይ የመሆን እድላቸዉ ከፍተኛ በመሆኑ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸዉ ሳይቀርቡ ከቀሩ በወ/መ/ስ/ስ/ህ/ቁጥር 161 ንዑስ ቁጥር 2 (ሀ) መሠረት በሌሉበት ክሱ እንዲታይ ማድረግ ሲገባ የስር ፍ/ቤት ክሱ እንዲቋረጥ ማድረጉ ህጋዊ መሠረት የሌለዉ ነው በማለት የስር ፍርድ ቤት የሰጠውን ብይን ሽሮታል።

በዚህም የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በታሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ፍሰሀ እሸቱ (ዶ/ር) የተከሰሱባቸዉ የወንጀል ክሶችን በሌሉበት የሚታይ አይደለም በማለት ክሱ እንዲቋረጥ የሰጠዉ ብይን የተሻረ መሆኑን በመረዳት ክሱን መስማት እንዲቀጥል ይፃፍ በማለት ችሎቱ ውሳኔ ሰጥቷል።

በታሪክ አዱኛ

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 13/02/2025

በመሰረታዊ ልብስ ስፌት የአሰልጣኞች ስልጠናን የተከታተሉ ሰራተኞች ሲመረቁ፤ ለ1 መቶ 50 የሕግ ታራሚዎች ደግሞ የጋርመንት ኢንዱስትሪ ስልጠና መስጠት ተጀመረ፡፡
አዲስ አበባ፡-የካቲት 7/2017 ዓ.ም (ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከሴንተር ፎር ጀስቲስ ጋር በመተባበር ከሁሉም ማረሚያ ማዕከል ተውጣጥተው የመሰረታዊ የልብስ ስፌት የአሰልጣኞች ስልጠናን የተከታተሉ 15 ሰራተኞች የካቲት 04 ቀን 2017ዓ.ም. አስመርቋል፡፡ ከምረቃው ጎን ለጎን በሴቶች እና በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል ለሚገኙ 150 የሕግ ታራሚዎች የጋርመንት ኢንዱስትሪ ስልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የልማትና ሥራ ፈጠራ ማቋቋም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን ኃ/ማርያም በመርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ሁሉም የሕግ ታራሚዎች ወደስራ እንዲገቡ ኮሚሽኑ አቅዶ እየሠራ ይገኛል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካ ታራሚዎችን በተለያዬ ሙያ እንዲሰለጥኑ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ሰልጣኞች ከምረቃ በኋላ የታራሚዎችን ዮኒፎርም እንዲሰፉ ይደረጋል ያሉት መሪ ሥራ አስፈፃሚው ለቀጣይ 21 ቀናት የሚሰጠውን ስልጠና በአግባቡ እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡
የሴንተር ፎር ጀስቲስ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኩምሳ ጉተታ በበኩላቸው ሰልጣኞች ስልጠናውን ሲከታተሉ ተቀጥሮ ለመስራት ሳይሆን የራሳቸውን ማሽን ገዝተው ከራሳቸው አልፈው ሌሎችን ቀጥሮ ለማሰራት ራዕይ ሰንቀው መሆን እንዳለበት አመላክተዋል፡፡
የሕግ ታራሚዎች ከእርምት ሲለቀቁ መሆን የሚፈልጉትን መወሰን ያለባቸው ዛሬ መሆኑን እንዳለበት የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ ማረሚያ ቤቱ ያመቻቸላቸውን የስልጠና ዕድል በአግባቡ እንዲጠቀሙበት አስገንዘበዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የጨርቃጨርቅ አልባሳት ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ተወካይ አቶ እሱባለው ገብሬ የሕግ ታራሚዎች አምራች ኃይል ሆነው እንዲወጡ ተቋማቸው 5 የመሠረታዊ ልብስ ስፌት አሰልጣኞችንና 1 አስተባባሪ መመደቡን ገልጸዋል፡፡
መንግስት የጋርመንት ኢንዱስትሪ ለማስፋፋት የያዘው ዕቅድ እንዲሳካ ታራሚዎች የሚሰጣቸውን ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው ለራሳቸውና ለሃገር ጠቃሚ እንዲሆኑ አደራ ብለዋል፡፡
ከሰልጣኞች መካከል የሕግ ታራሚ ታሪኩ ናግና የጋርመንት ስልጠና ዕድል በማግኘቱ መደሰቱን ገልጾ፤ የተሰጠውን ስልጠና ተጠቅሞ እራሱንና ቤተሰቦችን ለማገልገልና የበደላቸውን ወገኖች ለመካስ መዘጋጀቱን ተናግሯል፡፡

11/02/2025

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በምስራቅ ወለጋ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ በ27 ሰዎች ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ሀዘን ይገልፃል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ከኦሮሚያ ክልል ከሻምቡ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉዳያ ቢላ ወረዳ በመገልበጡ በደረሰው የትራፊክ አደጋ በ27 ሰዎች ህልፈተ ሕይወት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።

የሟች ቁጥር ከዚህ ሊበልጥ እንደሚችል መረጃ የሚያሳይ ሲሆን መሰል የትራፊክ አደጋዎች በቅርቡ በተለያዩ ሀገራችን አካባቢዎች ተከስተው የበርካታ ሰዎችን ሕይወት ከመንጠቃቸውም ባሻገር በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ትራፊክ ፖሊሶች፣ የትራንስፖርት ተቋማት፣ አሽከርካሪዎች፣ ኅብረተሰቡ እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመቀናጀት የትራፊክ ፍሰቱን ጤናማነት የሚያረጋግጥ በቴክኖሎጂ የታገዘ ከፍተኛ ቁጥጥር ካላደረጉ በስተቀር አስከፊውን የትራፊክ አደጋ ማስቆም ስለማይቻል በሰው ሕይወት እና በንብረት ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስና ለመቆጣጠር ይቻል ዘንድ ሁሉም በተሰለፈበት ሙያ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዚህ አጋጣሚ ጥሪውን ያቀርባል።

የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 11/02/2025

ኮሚሽኑ ከሀገሪቱ ሁለንተናዊ የዕድገት ፍላጎት ጋር በሚጣጣም መንገድ መጓዝ እንዲችል አመራሩ፣አባሉና ሰራተኛው በፈጠራ ታግዞ በተነሳሽነት በሁሉም ዘርፍ ውጤታማ ስራ መስራት እንደሚገባው ተገለጸ፡፡
ድሬዳዋ፡- የካቲት 4/2017 ዓ.ም (የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን)
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል በአምስት ዙሮች ለአመራሮች እና ለፈጻሚ ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው የስልጠና ማጠቃለያ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ማረሚያ ማዕከል ተከናውኗል፡፡
በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ ላይ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ጄኔራልን ጨምሮ ስትራቴጅክ አመራሮች ተገኝተው በአጠቃላይ በስልጠናው አፈጻጸም እና በማዕከሉ የስራ እንቅስቃሴ ዙርያ ከአባላት እና ሰራተኛው ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡
በዚሁ የስልጠና ማጠቃለያ ላይ እና በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ መሰረት አድርጎ በተካሄደ ውይይት የስራ መመሪያ የሰጡት ክቡር ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ መጀመርያ ላይ በሁሉም ማዕከላት የተደረገን ግምገማ መሰረት በማድረግ ክፍተቶች ከተለዩ በኃላ ለሁሉም አመራር እና ፈጻሚ ተደራሽ በሆነ መንገድ የተሰጠው ስልጠና ብዙ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን ከወዲሁ እያሳየ ነው፤ ብለዋል፡
ኮሚሽነር ጄኔራሉ አክለውም ከስልጠና በፊት የነበሩ የስነ ምግባር ችግሮች፣የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣የተከለከሉ ነገሮችን ማስገባት እና በየተሰማሩበት የስራ መስክ ውጤታማ አለመሆን፣ በብዙው የቀነሱ ቢሆንም በቀጣይ ስር ነቀል የሆነ ለውጥ እስኪመጣ ድረስ በትኩረት የሚሰሩ የቤት ስራዎቻችን ናቸው ፤ብለዋል፡፡
ኮሚሽር ጄኔራሉ በስራ መመሪያቸው ማረሚያ ኮሚሽን የሀገሪቱን ነባረዊ ሁኔታ መሰረት በማድረግ ከሌላው ተቋም ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆን በስነ ምግባሩ የተመሰገነ፣ተቀባይነት ያለው እና ለሌላው ምሳሌ ሊሆን የሚችል አባልና ሰራተኛ ሊፈጠር ይገባል ነው ፤ያሉት፡፡
የማዕከሉን የስልጠና አፈጻጸም አጭር ሪፖርት ያቀረቡት የማዕከሉ ዳይሬክተር ረዳት ኮሚሽነር ሙላት ጫንያለው እንዳሉት ከከፍተኛ አመራር ጀምሮ እስከፈጻሚ ደረስ በተሰጠው የ5 ዙሮች የስልጠና መርሃ ግብር በአጠቃላይ በማዕከል ደረጃ 443 የሰው ኃይል እንዲሰለጥን በማድረግ የነበሩ የአመለካከት እና የክህሎት ክፍተቶች እንዲሞሉ ጥረት ተደርጓል፤ ብለዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በስልጠና ሂደቱ ጨምሮ በአጠቃላይ በማዕከሉ ያሉ ጠንካሬዎችን እና ሊስተካከሉ ይገባቸዋል ፤ያሏቸውን ጥያቄዎች እና አስተያየቶች በስፋት አንስተው ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 06/02/2025

በወራቤ ማረሚያ ተቋም ለሶስት ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የግምገማ መድረክ ተጠናቀቀ ።

ጥር 29/2017 ዓ/ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የማረሚያ ቤቶች አሰተዳደር ኮሚሽን በተዘጋጀው ሠነድ በወራቤ ማረሚያ ተቋም ሲካሄድ የነበረው የግምገማ መድረክ ተጠናቋል ።

የስልጤ ዞን የፍትህ መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ በረከት ከድር በተገኙበት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የማረሚያ ቤቶች አሰተዳደር ኮሚሽን የተዘጋጀውን ለግምገማ መነሻ የሚሆን ሠነድ በኮማንደር ደሳለኝ ተደለ ለመድረኩ ቀርቦ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ግምገማ ሲካሄድበት ቆይቷል።

የግምገማ መድረኩ የመሩት ኮሚሽነር መሐመድ ጀማል እንደተናገሩት ተቋሙ በግምገማ መድረኩ የተነሱ ችግሮች በማረምና ቅንጅታዊ አስራሮችን በፊት ከነበረው የበለጠ በማዳበር የስራ ተግባራት በማስፍት ተቋሙ የክልሉ አምባሳደርነቱን ይዞ መቀጠል እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በየደረጃው ባሉ የተቋሙ አመራሮች የተካሄደው የግምገማ መድረክ በተቋሙ የተጀመረውን ሁለንተናዊ ለውጥ ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በዘላቂነት ለማስቀጠል መነቃቃትን የፈጠረ መድረክ እንደነበረ ተጠቅሷል።

በተቋሙ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች የአፈፃፀም ክፍተቶችን በማስተካከልና በማረም የመጡ ውጤቶችን በዘላቂነት በማረጋገጥ የህግ ታራሚዎችን በማረምና በማነፅ ሂደት አምራች ዜጋ ሆነው እንዲወጡ በሁሉም ዘርፍ መነቃቃትን የሚፈጥር የግምገማ መድረክ እንደነበር የተነሳ ሲሆን በየደረጃው ለሚገኘው አመራር በቀጣይ ስራዎችን በተሻለ ደረጃ ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አቅም የፈጠረ መሆኑም ተመላክቷል።

Photos from በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም  C/E Worabe Prison Institution 's post 01/02/2025

የህዝቡን ሰላም ለማወክ ጥረት የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አሳሰበ

ጥር 24/2017 )
በክልሉ በወቅታዊ የጸጥታና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ እየተካሔደ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በምክክር መድረኩ እንደገለጹት ክልሉ ተመስርቶ ወደ ተግባር ከገባበት ጊዜ ጀምሮ የህዝቡን ሰላም ለማወክ በግል እና በቡድን ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አካላት መኖራቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ ሰላም እንዳይኖር ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያን የማስፈጸሚያ መሳሪያ አድርገው በግል እና በቡድን የሚንቀሳቀሱ አካላት ስለመኖራቸውም ኃላፊው አስረድተዋል።

በክልሉ ህዝቦች መካከል መተማመን እንዳይኖር አንዱ ማህበረሰብ ሌላውን እንዲጠራጠር እና ለዘመናት በፍቅር፣በአንድነት እና በመተሳሰብ በሚኖሩ ህዝቦች መካከል ጠብ እንዲፈጠር እኩይ አላማቸውን ለማስፈጸም የሚጥሩ አካላት መኖራቸውን አቶ ተመስገን ተናግረዋል።

የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት በቅጥረኞቻቸው አማካኝነት በህዝቦች መካከል ጠብ በመፍጠር አላማቸውን ለማሳካት የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ኃላፊው አሳስበዋል።

የክልሉን ሰላም በአስተማማኝ ደረጃ ላይ ለማድረስ የጸጥታና የፍትህ ተቋማት የላቀ ጥረት ማድረግ አለባቸው ያሉት ኃላፊው የህዝብን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል የሚጥሩ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም አቶ ተመስገን አሳስበዋል።

የክልሉን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ክብር የሚነካ እና ባልተገባ መንገድ በመፈረጅ የጥላቻ ንግግር የሚያሰራጩ ወደ 600 የሚጠጉ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች መከፈታቸውን
ኃላፊው አመላክተዋል።

በክልሉ ከዚህ በፊት በጠብ ነጋዴዎች አማካኝነት በአንድ አንድ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር ማጋጠሙን ያስታወሱት ኃላፊው በህዝቡ፣በፖለቲካ አመራሩ እና በጸጥታ አካላት የላቀ ጥረት የህዝቡን ሰላም ወደ ነበረበት መመለስ መቻሉን አብራርተዋል።

ነገር ግን የክልሉ ሰላም እንዲቀለበስ ፍላጎት ያላቸው አካላት ዛሬም ያልተገባ እንቅስቃሴ እያደረጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

የክልሉ መንግስት የህዝቡን ሰላም አደጋ ላይ ለመጣል የሚጥሩ አካላትን ፈጽሞ ሊታገስ እንደማይችል አቶ ተመስገን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን በበኩላቸው የክልሉን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ ስራ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በየደረጃው ህዝቡ የሚያነሳቸው የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና ብልሹ አሰራሮችን ለመፍታት በትኩረት መስራት እንደሚገባም አቶ አክመል ጠቁመዋል።

በክልሉ ዘላቂ ሰላምን በማስፈን የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ይገባል ያሉት ኃላፊው በየደረጃው ያሉት የጸጥታና የፍትህ አካላት ሚናቸውን መወጣት የሚያስችል መድረክ መሆኑን አብራርተዋል።

በመድረኩ የጸጥታና የፍትህ መዋቅር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

Want your business to be the top-listed Government Service in Addis Ababa?

Click here to claim your Sponsored Listing.

Location

Website

Address


Addis Ababa