የሚሰሩ እጆች ወግ ዶክመንተሪ
ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁን
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://aabols.gov.et/qr.html
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ- Addis Ababa Labor and Skill Bureau
በክህሎት የበለፀገ እና ሥራን ባህሉ ያደረገ ትውልድ ለኢትዮጵያችን ብልፅግና መሠረት ነው!!
08/06/2026
08/06/2026
ከተረጂነት ወደ ምርታማነት
06/06/2026
ምርጫውን ለማደናቀፍ የተደረገው ጥረት በሕዝብ እና በጸጥታ አካላት ቅንጅት ከሽፏል፡- የሰላም ሚኒስቴር
በኢትዮጵያ የተካሄደውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍና የሕዝብን ሰላም ለማደፍረስ ጽንፈኛ ኃይሎችና የውጭ ጠላቶች የከፈቱት ሁለንተናዊ ጥቃት መክሸፉን የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ ሀገራዊ ለውጡን የማይቀበሉ አካላት በመሬት ላይ የሽብር ጥቃቶችን ከመፈጸም ጀምሮ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የፕሮፓጋንዳና የሥነ-ልቦና ጦርነት ሲያካሂዱ ቆይተዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ምርጫውን የህልውና እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማረጋገጫ አድርጎ በመውሰድ በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ በአንጻሩ የስልጣን ሽግግርን በድምጽ መስጫ ኮሮጆ ሳይሆን በኃይል ለመጠቅለል የሚሹ የውስጥ ቅጥረኞችና የኢትዮጵያን እድገት የማይፈልጉ የውጭ ኃይሎች ሂደቱን ለማስቆም ከምርጫው በፊት፣ ወቅትና በኋላ ከፍተኛ ሴራዎችን መሸረባቸውን ይፋ አድርጓል።
አፍራሽ ኃይሎቹ የመንግሥትን ሕጋዊ ቅቡልነት ለማሳጣትና ኢትዮጵያን ወደ ሥርዓት አልበኝነት ለመክተት ሕዝቡ የምርጫ ካርድ እንዳይወስድ፣ በፖለቲካ ድጋፍ ሰልፎች ላይ እንዳይገኝ እና በምርጫው ቀን ድምጽ እንዳይሰጥ ቅስቀሳ ሲያደርጉ እንደነበር ተጠቅሷል።
ሆኖም የኢትዮጵያ ህሕብ ለጥሪዎቻቸው እውቅና ባለመስጠትና የጽንፈኝነትን አጀንዳ ውድቅ በማድረግ፥ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ተሳትፎ የምርጫ ካርድ በመውሰድ፣ በሰልፎች ላይ በነጻነት በመገኘትና በምርጫው ቀን በነቂስ ወጥቶ ድምጽ በመስጠት አፍራሽ ኃይሎቹን ማሸነፉን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ይህ የዲሞክራሲ ስኬት ያለመስዋዕትነት እንዳልመጣ የጠቀሰው የሰላም ሚኒስቴር፤ የጸጥታ ተቋማት ባደረጉት ወቅቱን የጠበቀና የተቀናጀ አጸፋዊ እርምጃ የሽብር ዕቅዶቹ ሊከሽፉ መቻላቸውን አስታውቋል።
ሆኖም የሕዝቡን አብሮነት ለመስበር የተሞከሩ የሽብር ጥቃቶች እንደነበሩ ጠቅሶ፤ ህዝቡ የከፈለው መስዋዕትነት ጽንፈኝነትን በመቃወም ሀገርን የሚያስቀጥል ሕጋዊ መንግስት ለመመስረት ያለውን ጽኑ ፍላጎት ያሳየበት መሆኑም ተመልክቷል።
AMN
06/06/2026
በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚደረገው የስፖርት ፌስቲቫል በስኬት እንዲከናወን የሚመለከታቸው አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
***
በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚደረገውን የስፖርት ፌስቲቫል አስመልክቶ የፀጥታ ተቋማት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡
ፌስቲቫሉ በተያዘው እቅድ መሰረት ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የፀጥታ አካላት ካደረጉት ዝግጅት በተጨማሪ የፕሮግራሙ አዘጋጆች እና ታዳሚዎች የሚኖራቸው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል፡፡
ስፖርት ወንድማማችነት እና አብሮነት ከሚገለፅባቸው ዘርፎች አንዱ መሆኑን ፖሊስ አስታውሶ ስፖርታዊ ፌስቲቫሉ የከተማችንን መልካም ገጽታ በሚገነባ እና ስፖርታዊ ጨዋነትን በተላበሰ መልኩ ሊካሄድ እንደሚገባ አሳስቧል፡፡
የፕሮግራሙ አዘጋጆች ከፀጥታ አካላት ጋር በጋራ እየሰሩ ነው፡፡ የዝግጅቱ ታዳሚዎች ፕሮግራሙ በሠላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ኃላፊነት ያለባችሁ በመሆኑ ከፖሊስ ጋር ተባብራችሁ መስራት ይጠበቅባችኋል፡፡ ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ ስለሚኖር ለፍተሻ መተባበር እና ወደ ፌስቲቫሉ ስፍራ የማይገቡ ቁሳቁሶችን ባለመያዝ ሁሉም ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል።
ፌስቲቫሉ በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
ህብረተሰቡ ማንኛውም ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) EFPApp በመጠቀም ጥቆማ መስጠት እንደሚገባም ጥሪ ተላልፏል።
*
Click here to claim your Sponsored Listing.
Location
Category
Contact the business
Website
Address
5 Kilo
Addis Ababa
