04/05/2020
የካራማራው ጦርነት (የተጠናቀቀው የካቲት 26/ 1970 ዓ.ም ነበር)
ጓድ ሊቀመንበር መንግስቱ ሃ/ማርያም ይሄን ብለው ነበር;-
‹‹…ታፍራና ተከብራ የኖረች ኢትዮጵያ ተደፍራለች፡፡ በአሁኑ ሰዓት የአብዮታዊት እናት አገራችን ዳር ድንበርና የማይገሰሰው አንድነታችን በውጭ ኃይል እየተደፈረ ነው፡፡ በአብዮታችንና በአንድነታችን በጠቅላላው በብሔራዊ ኅልውናችን ላይ የሚደረገው ወረራና ድፍረት እጅግ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ደርሷል… ለብዙ ሺሕ ዘመናት አስከብሮን የኖረው አኩሪ ታሪካችን በዚህ አብዮታዊ አዲስ ትውልድ ጊዜ መጉደፍ የለበትም፡፡ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ክብርንና ነፃነትህን ለመድፈር፣ አገርህን ለመቁረስ… የተጀመረውን ጣልቃ ገብነትና ወረራ ከመለዮ ለባሹ ጋር ተሠልፈህ ለመደምሰስ የምትዘጋጅበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ተነስ! ታጠቅ! ዝመት! ተዋጋ! እናሸንፋለን!!››
የጓድ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ተነስ ታጠቅ ዝመትን ተከትሎ ታጠቅ የጦር ሠፈር በተባለው ቦታ ለሦስት ወራት የሠለጠነው 300 ሺሕ ሚሊሺያ (ሕዝባዊ ሠራዊት) ከመደበኛው ጦር ጋር ሆኖ በአብዮት አደባባይ ታላቅ ሠልፍ አሳየ፡፡

27/09/2019
21/01/2019