12/06/2026
"ውድ ኢትዮጵያውያን ለ5 ሚሊዮን ኮደሮች ምዕራፍ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ!
በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። የ«5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች» ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማት እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሰልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ስልጠናውን አጠናቀዋል። ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው።
በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ ነው። እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም. ድረስ የሰልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፥ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።
ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው። ጊዜያችሁን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥባችሁ፤ በመመዝገብና በመማር ወደ ትምህርት ገበታችሁ ስትመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳትሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላችሁ የዲጂታል መሪዎች እንድትሆኑ አሳስባለሁ። ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፥ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው።
የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!"
ክቡር የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ:
ethiocoders.et/
12/06/2026
H.E. Ms. Demitu Hambissa Bonsa, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary of Ethiopia to Italy and Permanent Representative to FAO, IFAD, and WFP, confers with IFAD President Álvaro Lario.
The high-level discussion focused on transforming rural livelihoods, scaling up climate-smart farming, and boosting investments for young agricultural innovators in Ethiopia. Both sides reiterated their commitment to turning climate challenges into sustainable economic opportunities for millions of smallholder farmers.
10/06/2026
በጣሊያን ካሲኖ ዩኒቨርሲቲ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ከኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጋር ውይይት ተካሄደ
========
(ሰኔ 02/2018 ዓ.ም.) በሮም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ ከጣሊያን ካሲኖ ዩኒቨርሲቲ ጋር ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጠናከርና የቀጣይ የOutreach ፕሮግራም ትግበራ መሰረት ለመጣል ያለመ የውይይት መድረክ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትና አመራሮች፣ የተማሪ ተወካዮች እንዲሁም ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በታደሙበት በዩኒቨርሲቲው ግቢ ተካሂዷል።
በጣሊያን በሚገኙ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከአንድ ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በትምህርት ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ካሲኖ ዩኒቨርሲቲ 394 ተማሪዎችን በማስተናገድ ትልቁን ቁጥር ይይዛል።
በዕለቱ በጣሊያን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ክብርት ደሚቱ ሃምቢሳ ወቅታዊ የአገራችንን ጉዳዮች በማንሳት፣ ኢትዮጵያ በልማት ጎዳና ላይ የምትገኝ መሆኗን ገልጸው፣ በውጭ የትምህርት ዕድል ያገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀት፣ ልምድና ቴክኖሎጂ ወደ አገር ቤት በማሸጋገር ለአገር ልማትና ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ የቆንስላ አገልግሎትና አሰራር እንዲሁም አገልግሎቱን በቅርበት ለተማሪዎቹ ተደራሽ የሚሆንበት ሁኔታ ለመክፈት ይህ ቀን የመጀመሪያውን ስራ የሚከናወንበት መሆኑን በመጥቀስ ኤምባሲው ለተማሪዎች የሚያስፈልገውን እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አምባሳደሯ ያለቸውን ሙሉ እምነት አንስተዋል::
የካሲኖ ዩኒቨርሲቲ ሬክተር ፕሮፌሰር ማርኮ ዴል ኢዞላ (Prof. Marco Dell'Isola) በበኩላቸው፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ለኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የነጻ ትምህርት ዕድል በማመቻቸት በቅርበት እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ ለወደፊትም በጋራ መሥራት በሚገቡ ጉዳዮችና በዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ የአገልግሎት እንቅስቃሴ ላይ ገለጻ አድርገዋል። ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በትምህርታቸው ጠንካራና መልካም ሥነ-ምግባር ያላቸው መሆናቸውን በማድነቅ፣ ይህ ዕድል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ያላቸውን ተስፋ ጠቁመዋል።
በመድረኩ ማጠቃለያም አገልግሎት ለሚፈልጉ ተማሪዎች የቆንስላ አገልግሎት በቦታው ተደራሽ ማድረግ ተችሏል።
05/06/2026
Representing one of Africa’s largest livestock sectors, H.E Demitu Hambisa Bosa, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary of Ethiopia to Italy and Permanent Representative to FAO, IFAD, and WFP, shared powerful, field-tested lessons on transitioning smallholder farmers away from antimicrobial reliance while protecting production and livelihoods.
She shared her insightful message during a crucial panel exploring "The Future of Antimicrobial Use in Livestock: The Economic Cost of Action or Inaction" hosted by the Food and Agriculture Organization (FAO) in Rome.